ለካ ፡ እግዚአብሔር ፡ እያለ (Leka Egziabhier Eyale) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 3.jpg


(3)

የናርዶስ ፡ ሽቶዬ
(Yenardos Shetoyie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2014)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 6:05
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

አዝለካ ፡ እግዚአብሔር ፡ እያለ
ለካ ፡ አምላኬ ፡ እያለ (፪x)
አይቆረጥም ፡ ተስፋ
ምኑ ፡ ሁኔታ ፡ ቢከፋ
ኧረ ፡ አይቆረጥም ፡ ተስፋ
ምኑ ፡ ሁኔታ ፡ ቢከፋ

ጥበበኛው ፡ እያለ
ኤልሻዳዩ ፡ እያለ
ሁሉን ፡ ቻዩ ፡ እያለ
ተዓምረኛው ፡ እያለ

አይወራም ፡ ስንፍና
እርሱ ፡ ጌታ ፡ ነውና
ኧረ ፡ አይወራም ፡ ስንፍና
እርሱ ፡ ንጉሥ ፡ ነውና
እርሱ ፡ ጌታ ፡ ነውና
እርሱ ፡ ንጉሥ ፡ ነውና
እርሱ ፡ አምላክ ፡ ነውና
እርሱ ፡ ገዢ ፡ ነውና

ባይዘንብ ፡ ዝናቡ ፡ ባይነፍስ ፡ ንፋሱ
እግዚአብሔር ፡ ያለው ፡ ቀን ፡ አይቀረም ፡ መድረሱ (፪x)
በክብሩ ፡ ማለፊያ ፡ ብሥራውም ፡ ድንቅ
ከአንደበቱ ፡ ቃል ፡ አንዳችም ፡ አይውድቅም
በክብሩ ፡ ማለፊያ ፡ ብሥራውም ፡ ድንቅ
ከአንደበቱ ፡ ቃል ፡ አንዳችም ፡ አይውድቅም

አዝለካ ፡ እግዚአብሔር ፡ እያለ
ለካ ፡ አምላኬ ፡ እያለ (፪x)
አይቆረጥም ፡ ተስፋ
ምኑ ፡ ሁኔታ ፡ ቢከፋ
ኧረ ፡ አይቆረጥም ፡ ተስፋ
ምኑ ፡ ሁኔታ ፡ ቢከፋ

ጥበበኛው ፡ እያለ
ኤልሻዳዩ ፡ እያለ
ሁሉን ፡ ቻዩ ፡ እያለ
ተዓምረኛው ፡ እያለ

አይወራም ፡ ስንፍና
እርሱ ፡ ጌታ ፡ ነውና
ኧረ ፡ አይወራም ፡ ስንፍና
እርሱ ፡ ንጉሥ ፡ ነውና
እርሱ ፡ ጌታ ፡ ነውና
እርሱ ፡ ንጉሥ ፡ ነውና
እርሱ ፡ አምላክ ፡ ነውና
እርሱ ፡ ገዢ ፡ ነውና

የፃድቁ ፡ ጩኸት ፡ መች ፡ በከንቱ ፡ ይቀራል
በትንሳኤው ፡ ማግስት ፡ በድል ፡ ይቀየራል (፪x)
ከፈተናው ፡ ጋራ ፡ መውጫውን ፡ አድርጐ
ሲያመልስ ፡ አይተናል ፡ የሄድውን ፡ ምርኮ
ከፈተናው ፡ ጋራ ፡ መውጫውን ፡ አድርጐ
ሲያመልስ ፡ አይተናል ፡ የሄድውን ፡ ምርኮ

በእግዚአብሔር ፡ ደስ ፡ ይበልህ
የልብህን ፡ መሻት ፡ ይሰጥሃል (፪x)
ፅድቁን ፡ መንግስቱን ፡ እሻ
ሁሉ ፡ ይጨመርልሃል (፪x) [1]

ታማኝ ፡ ነው ፡ ተስፋ ፡ የሰጠው
በፍፁም ፡ ግድፍ ፡ ጉድለት ፡ የለውም
አደራ ፡ ስጠው ፡ መንገድህን
ያቀናል ፡ ጐዳናህን (፫x)

  1. ማቴዮስ ፮ ፡ ፴፫ (Matthew 6:33)