ክቡርና ፡ ቅዱስ ፡ ነው (Kiburena Qidus New) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 1.jpg


(1)

ኃይልንም ፡ የሚያስታጥቀኝ
(Hailenem Yemiyastateqegn)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፪ (2000)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

 
ፅድቅና ፡ መንግሥትህ ፡ እንደምን ፡ ያምራሉ
ከአንተ ፡ ወድያ ፡ ሕይወት ፡ ለምን ፡ ያሰኛሉ
የአባትነትህ ፡ ፍቅርህ ፡ በኢየሱስ ፡ ያየነው
ማርኮ ፡ አስቀርቶናል ፡ ኑሮዋችን ፡ የአንተ ፡ ነው (፪x)

አዝ:- ክቡርና ፡ ቅዱስ ፡ ኃያል
ልዑል ፡ አባት ፡ እግዚአብሔር
ከአንተ ፡ በቀር ፡ ማንም ፡ የለም
አልነበረም ፡ ደግሞ ፡ አይኖርም (፪x)
 
ሥራህን ፡ እያየን ፡ እናደንቅሀለን
ሁልጊዜ ፡ ፍቅርህን ፡ ጌታ ፡ እናስባለን
መንፈስና ፡ ሥጋ ፡ ነፍሳችን ፡ ተስማምተው
ያመሰግኑሃል ፡ ክበር ፡ ጌታ ፡ ብለው (፪x)
 
አዝ:- ክቡርና ፡ ቅዱስ ፡ ኃያል
ልዑል ፡ አባት ፡ እግዚአብሔር
ከአንተ ፡ በቀር ፡ ማንም ፡ የለም
አልነበረም ፡ ደግሞ ፡ አይኖርም (፪x)
 
ውለታህ ፡ አለብን ፡ ከልብ ፡ የማይጠፋ
እኛን ፡ የረዳኸን ፡ ኢየሱስ ፡ ክብርህ ፡ ይስፋ
ከቶ ፡ ምን ፡ አለና ፡ ለእኛ ፡ ያላደረከው
መድኃኒታችን ፡ ሆይ ፡ ክብራችን ፡ ከአንተ ፡ ነው (፪x)
 
አዝ:- ክቡርና ፡ ቅዱስ ፡ ኃያል
ልዑል ፡ አባት ፡ እግዚአብሔር
ከአንተ ፡ በቀር ፡ ማንም ፡ የለም
አልነበረም ፡ ደግሞ ፡ አይኖርም (፪x)
 
ከፀሐይ ፡ ሰባት ፡ እጅ ፡ ድምቀህ ፡ ትታያለህ
ሁለንተናህ ፡ ውብ ፡ ነው ፡ ምንም ፡ አልጐደለህ
ለግርማዊነትህ ፡ ክብር ፡ እንሰግዳለን
ልዑል ፡ ሆይ ፡ ለሥምህ ፡ እንዘምራለን (፪x)
 
አዝ:- ክቡርና ፡ ቅዱስ ፡ ኃያል
ልዑል ፡ አባት ፡ እግዚአብሔር
ከአንተ ፡ በቀር ፡ ማንም ፡ የለም
አልነበረም ፡ ደግሞ ፡ አይኖርም (፬x)

ከአንተ ፡ በቀር ፡ ማንም ፡ የለም
አልነበረም ፡ ደግሞ ፡ አይኖርም (፪x)

አዝ:- ክቡርና ፡ ቅዱስ ፡ ኃያል
ልዑል ፡ አባት ፡ እግዚአብሔር
ከአንተ ፡ በቀር ፡ ማንም ፡ የለም
አልነበረም ፡ ደግሞ ፡ አይኖርም (፪x)