እወድሃለሁ (Ewedihalehu) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 1.jpg


(1)

ኃይልንም ፡ የሚያስታጥቀኝ
(Hailenem Yemiyastateqegn)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፪ (2000)
ቁጥር (Track):

(3)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

 
እወድሃለሁ ፡ አጅግ ፡ አብዝቼ
ከልቤ ፡ ጋራ ፡ እጄን ፡ አንስቼ
በምን ፡ ቋንቋ ፡ ነው ፡ ከቶ ፡ ምገልጸው
የልቤ ፡ አምላክ ፡ ሆይ ፡ ፍቅርህ ፡ ብርቱ ፡ ነው (፪x)
 
አዝ፦ ቃላት ፡ ባገኘሁና
ባወራው ፡ የአንተን ፡ ምስጋና
የልቤ ፡ በደረሰልኝ
አምላኬ ፡ አንተው ፡ ከብረህልኝ
 
የሚያስፈልገኝ ፡ አንድ ፡ ነገር
እርሱም ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ ጌታ ፡ እግዚአብሔር
አንተን ፡ ካገኘሁ ፡ ጠግቤ ፡ አድራለሁ
ስለዚህ ፡ አምላኬ ፡ እወድሃለሁ (፪x)

አዝ፦ ቃላት ፡ ባገኘሁና
ባወራው ፡ የአንተን ፡ ምስጋና
የልቤ ፡ በደረሰልኝ
አምላኬ ፡ አንተው ፡ ከብረህልኝ

መላ ፡ እኔነቴ ፡ አንተን ፡ ይወዳል
በቀን ፡ በለሊት ፡ ልቤ ፡ ያስብሃል
ያላንተ ፡ መኖር ፡ አይሆንልኝም
ሕይወቴ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ሌላም ፡ የለኝም (፪x)

አዝ፦ ቃላት ፡ ባገኘሁና
ባወራው ፡ የአንተን ፡ ምስጋና
የልቤ ፡ በደረሰልኝ
አምላኬ ፡ አንተው ፡ ከብረህልኝ

የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ መድህኔ
ሕይወቴ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለእኔ (፪x)

ሕይወት ፡ ተገለጠ ፡ እኔም ፡ አይቻለሁ
ጌታ ፡ ቸር ፡ መሆኑን ፡ ቀምሼ ፡ አውቄያለሁ
እግዚአብሔር ፡ አምላክ ፡ ነው ፡ እኔም ፡ በርቶልኛል
ታዲያ ፡ ከእርሱ ፡ ፍቅር ፡ ማንስ ፡ ይለየኛል
 
አዝ፦ የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ መድህኔ
ሕይወቴ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለእኔ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ መድህኔ
ሰላሜ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለእኔ
 
ሰው ፡ አንተን ፡ ካገኘ ፡ ምን ፡ ያስፈልገዋል
እፎይ ፡ ብሎ ፡ አርፎ ፡ ተደላድሎ ፡ ይኖራል
ፍቅርህ ፡ የሚያጠገብ ፡ ልብን ፡ የሚያረካ
የመኖር ፡ ትርጉሙ ፡ ጌታ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ለካ
 
አዝየእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ መድህኔ
ሕይወቴ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለእኔ
(፪x)
ዕረፍቴ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለእኔ
ሰላሜ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ለእኔ