ከፍታዬ ፡ ኢየሱስ (Kefetayie Eyesus) - ካሳሁን ፡ ለማ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ካሳሁን ፡ ለማ
(Kassahun Lemma)

Kasahun Lema 3.jpg


(3)

አቀላልቷል ፡ ሰማዩ
(Aqelaltual Semayu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2011)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የካሳሁን ፡ ለማ ፡ አልበሞች
(Albums by Kassahun Lemma)

 
እግዚአብሔር ፡ በድንቅ ፡ የረዳው (ኧረ ፡ እንደ ፡ እኔስ ፡ ማነው) (፫x)
ሞቷል ፡ ሲባል ፡ ሕይወት ፡ ያየ ፡ ሰዉ (ኧረ ፡ እንደ ፡ እኔስ ፡ ማነው) (፫x)
የጠላቱን ፡ ውድቀት ፡ ያየ ፡ ሰዉ (ኧረ ፡ እንደ ፡ እኔስ ፡ ማነው) (፫x)
ጌታ ፡ ከላይ ፡ ተሻገር ፡ ያለዉ (ኧረ ፡ እንደ ፡ እኔስ ፡ ማነው) (፫x)

እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነው ፡ ቢኮሩበት ፡ ያኮራል
ስሙ ፡ ከስም ፡ በላይ ፡ ነው ፡ ሲጠሩት ፡ ያስመልጣል
ኮራ ፡ ብዪ ፡ እኖራለሁ ፡ ያመንኩትን ፡ አውቃለሁ
ሹመቴ ፡ ሽልማቴ ፡ ከፍታዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው

አዝ፦ ከፍታዬ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ከፍታዬ (፬x)

ምሥጋና ፡ አለኝ ፡ ልቤ ፡ ተነሳ (እንደገና) (፫x)
በእርሱ ፡ ያለፍኩትን ፡ ያን ፡ ቀን ፡ አሰበና (እንደገና) (፪x)
አምልኮ ፡ አለኝ ፡ ልቤ ፡ ተነሳ (እንደገና) (፫x)
እርሱ ፡ ያደረገልኝን ፡ ዉለታ ፡ አሰበና (እንደገና) (፪x)

ገና ፡ አለኝ ፡ እኔስ ፡ ገና
ለአንተ ፡ ብዙ ፡ ምሥጋና
ዉለታህ ፡ አለብኝና (፪x)
ዉለታ ፡ አለብኝና (፰x)

ያየሁትን ፡ ሳላይ ፡ አልቀርም ፡ መንገድ ፡ ላይ
እደርሳለሁ ፡ ከግቤ ፡ ህልም ፡ አለኝ ፡ ከሰማይ
ሰው ፡ አይደለምና ፡ የተናገረኝ
የጠራኝ ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ ቃሉን ፡ የሰጠኝ

ዮሴፍ ፡ በሕይወት ፡ አለ ፡ ያውም ፡ በክብር
ራዕዩን ፡ የሰጠ ፡ አለና ፡ እግዚአብሔር
ሰረገላው ፡ ከደጅ ፡ ቆሟል ፡ ለማስረጃ
ይሄው ፡ ዘመን ፡ መጣ ፡ ወደክብር ፡ መውጫ

አዝ፦ ከፍታዬ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ከፍታዬ (፬x)

ዓለም ፡ ሳይፈጠር ፡ በልጁ ፡ ወዶኛል
ልክደው ፡ የማልችለው ፡ ይህ ፡ እውነት ፡ ገብቶኛል
የብረቱ ፡ መዝጊያ ፡ ምን ፡ ቢቆም ፡ ከፊቴ
አውቆ ፡ ይከፈታል ፡ ጌታ ፡ አለ ፡ ከፊቴ

ንጉሥ ፡ የወርቁን ፡ ዘንግ ፡ ዘረጋልኝና
ያለህግ ፡ አስገባኝ ፡ ከፋፈተውና
ገና ፡ ሳልናገር ፡ ሁሉ ፡ ተሰካካ
የታመንኩት ፡ አምላክ ፡ ቀድሞ ፡ ወጥቷል ፡ ለካ

አዝ፦ ከፍታዬ ፡ ነው ፡ ጌታ ፡ ከፍታዬ (፬x)