ቅዱስ ፡ እግዚአብሔር (Qedus Egziabhier) - ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን
(Kalkidan Tilahun)

Kalkidan Tilahun 5.jpg


(5)

ለእግዚአብሔር ፡ ቀላል ፡ ነው
(LeEgziabhier Qelal New)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 7:33
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቃልኪዳን ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Kalkidan Tilahun)

ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ እግዚአብሔር
ንጹህ ፡ ፍፁም ፡ ነውር ፡ የሌለህ (፪x)

አንተ ፡ ነውር ፡ የለህም
አንተ ፡ እድፈት ፡ የለህም
አንተ ፡ ጉድለት ፡ የለህም
አንተ ፡ እንከን ፡ የለህም (፪x)

አንተ ፡ ራስህ ፡ እውነት ፡ ነህ
ምንም ፡ ውሸት ፡ የለብህ
ኦ ፡ የለብህ (፪x)

ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ እግዚአብሔር
ንጹህ ፡ ፍፁም ፡ ነውር ፡ የሌለህ (፪x)

አንተ ፡ ነውር ፡ የለህም
አንተ ፡ እድፈት ፡ የለህም
አንተ ፡ ጉድለት ፡ የለህም
አንተ ፡ እንከን ፡ የለህም (፪x)

ታድያ ፡ እኔ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
እግዚአብሔር ፡ አይደለም ፡ ዎይ (፪x)
አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
እግዚአብሔር ፡ አይደለም ፡ ዎይ (፪x)

ጠቢብ ፡ በጥበቡ ፡ አይመካ
ኃያልም ፡ በኃይሉ ፡ አይመካ
ፍርድንና ፡ ጽድቅን ፡ በምድር ፡ ላይ ፡ የሚያደርግ
እርሱ ፡ መሆኑን ፡ በማወቁ ፡ ብቻ
በዚያ ፡ ይመካ (፪x)

አውቄያለሁና ፡ ጠንቅቄ
ያላንተ ፡ ተስፋ ፡ እንደሌለኝ
ያላንተ ፡ ተስፋ ፡ እንደሌለኝ (፪x)

አንተን ፡ የታመነ ፡ ሰው ፡ ሌላ ፡ ሌላ ፡ ሳይደምር/ሳይጨምር
የተረጋገጠ ፡ ነው ፡ ፍጻሜው ፡ እንደሚያምር (፪x)

ታድያ ፡ እኔ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
እግዚአብሔር ፡ አይደለም ፡ ዎይ (፪x)
አሁንስ ፡ ተስፋዬ ፡ ማነው
እግዚአብሔር ፡ አይደለም ፡ ዎይ (፪x)

አዋቂው ፡ በዕውቀቱ ፡ አይመካ
ጻድቁም ፡ በጽድቁ ፡ አይመካ
ፀላይም ፡ በፀሎቱ ፡ አይመካ
ጿሚዉም ፡ በመጾሙ ፡ አይመካ
ፍርድንና ፡ ጽድቅን ፡ በምድር ፡ ላይ ፡ የሚያደርግ
እርሱ ፡ መሆኑን ፡ በማወቁ ፡ ብቻ
በእርሱ ፡ ይመካ (፪x)

ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ እግዚአብሔር
ንጹህ ፡ ፍፁም ፡ ነውር ፡ የሌለህ (፪x)

አንተ ፡ ነውር ፡ የለህም
አንተ ፡ እድፈት ፡ የለህም
አንተ ፡ ጉድለት ፡ የለህም
አንተ ፡ እንከን ፡ የለህም (፪x)

አንተ ፡ ራስህ ፡ እውነት ፡ ነህ
ምንም ፡ ውሸት ፡ የለብህ
ኦ ፡ የለብህ (፪x)