Kalkidan Tilahun/Beyet Hager New Egziabhier/Ejeg Yemimer

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ዘማሪ ቃልኪዳን ጥላሁን ሌላ ሥም ሊሊ ርዕስ እጅግ የሚምር አልበም በየት ሃገር ነው እግዚአብሔር

ጻድቅ ነህ ጌታ ስራህ ትክክል የማታደላ የማትበድል ለታላቅነትህ ፍጻሜ የለው አቤት ጌታም ሆይ ስራህ ድንቅ ነው

ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜ ምሥጋናህን ይናገራል (፫x) ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜ ምሥጋናህን ይናገራል (፫x)

ደግሜ ደጋግሜ እባርክሃለሁ ምሥጋና ዘወትር ዘወትር በአፌ ነው ማለዳ በምሥጋና አፌን እከፍታለሁ ከአንደበቴ ፍሬ ለአንተው እነግራለሁ

ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜ ምሥጋናህን ይናገራል (፫x) ምላሴ ጽድቅህን ሁልጊዜ ምሥጋናህን ይናገራል (፫x)

አዝ እጅግ የሚምር የሚራራ አምላክ ነውና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና (፪x)

እንኳንስ ምረሄኝ ቀርቶልኝ አበሳ (፪x) እኔስ ምሥጋናዬን ሁልጊዜው አልረሳ (፪x) ምህረትህ በእኔ ላይ ጠንክራለችና (፪x) ኃይሌ ታድሶልኝ ቆምኩኝ እንደገና (፪x)

አዝ እጅግ የሚምር የሚራራ አምላክ ነውና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና (፬x)

ማዳኑን አስታውቆ ጽድቁንም ገለጠ (፪x) ከእኛ መተላለፍ ምህረቱ በለጠ (፪x) በሞገሱ ጋሻ እየከለለን (፪x) ከአዳነን በኋላ ምህረቱ ያዘን (፪x)

አንድ ላይ ተስማሙ እውነትና ምህረት (፪x) መግባትም ተቻለን እግዚአብሔር ካለበት (፪x) ጻድቅ ፈራጅ ሲሆን እንከን የሌለበት (፪x) አልፈረደብኝም ምህረቱ አይሎበት (፪x)

አዝ እጅግ የሚምር የሚራራ አምላክ ነውና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና የእኔ ጌታ ይድረሰው ምሥጋና (፬x)

ጌታ እልሃለሁ አንተን አመልካለሁ (፪x) አምላክ እልሃለሁኝ አንተን አመልካለሁ (፪x) አንተን አመልካለሁ አንተን አመልካለሁ (፪x)

ይገባሃል የአንደበቴ ቃል ይገባሃል የአፌ ምሥጋና ይገባሃል ልዘምርልህ ይገባሃል ላገለግልህ

እኔ አምላክ እልሃለሁኝ አንተን አመልካለሁ (፭x) እስከዛሬ ተመስገን ብያለሁ ተባረክ ብያለሁ አሃ ከፍ በል ብያለሁ እስከዛሬ ተመስገን ብያለሁ ተባረክ ብያለሁ አሃ ከፍ በል ብያለሁ

ደግሞ ዛሬ ዛሬ ምን ልበል ዛሬ ምን ልበል ደግሞ አሁን አሁን ምን ልበል ጌታ አሁን ምን ልበል ደግሞ ዛሬ ዛሬ ምን ልበል ዛሬ ምን ልበል ዛሬ ምን ልበል

ይገባሃል የአንደበቴ ቃል ይገባሃል የአፌ ምሥጋና ይገባሃል ላገለግልህ ይገባሃል ልዘምርልህ

ሃሌሉያ ሃሌሉያ (፬x) ሃሌሉያ ሃሌሉያ (፬x) ሃሌሉያ ሃሌሉያ (፬x)