ትክክል ፡ ነው (Tekekel New) - ቃለአብ ፡ ፀጋዬ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቃለአብ ፡ ፀጋዬ
(Kaleab Tsegaye)

Kaleab Tsegaye 1.jpeg


(1)

እንዲህም ፡ አለ
(Endihem Ale)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2011)
ቁጥር (Track):

(Track)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቃለአብ ፡ ፀጋዬ ፡ አልበሞች
(Albums by Kaleab Tsegaye)

ቢሆንም ፡ ባይሆንም ፡ አምልኮዬን ፡ አላቆምም (፪x)

አዳዲስ ፡ መዝሙር ፡ ለእርሱ ፡ ነውና ፡ (ምሥጋና ፡ ምሥጋና)
ለታላቅነቱ ፡ (ምሥጋና ፡ ምሥጋና) (፪x)

ታሞ ፡ አዘነ ፡ ሞቶ ፡ አለቀሰ
የሰው ፡ እርዳታ ፡ መች ፡ ከዚህ ፡ አለፈ
ሲታመም ፡ ቀርቶ ፡ ሞቶ ፡ ቢደርስ
ሬሳ ፡ አይተናል ፡ ሲቀሰቀስ

ቢሆንም ፡ ባይሆንም ፡ አምልኮዬን ፡ አላቆምም (፪x)

የቤቱን ፡ ትልቅ ፡ ኤልያብን ፡ ትቶ
ቀቡልኝ ፡ ካለ ፡ እረኛውን ፡ ጠርቶ
ያዕቆብን ፡ ወዶ ፡ ኤሳውን ፡ ከጠላ
ሲረፍድ ፡ ይገባል ፡ የጌታ ፡ ስራ

ትክክል ፡ ነው ፡ ትክክል ፡ ነው (፮x)

የሰማይ ፡ መስኮት ፡ ቢከፈት ፡ እንኳን
በአንድ ፡ ቀን ፡ ይሄ ፡ እንዴት ፡ ይሆናል
ንጉሡ ፡ እምቢ ፡ ቢል ፡ ትንቢት ፡ አዳምጦ
ሳይበላ ፡ ሞተ ፡ በሰው ፡ ተረግጦ

ቢሆንም ፡ ባይሆንም ፡ አምልኮዬን ፡ አላቆምም (፪x)

አዳዲስ ፡ መዝሙር ፡ ለእርሱ ፡ ነውና ፡ (ምሥጋና ፡ ምሥጋና)
ለታላቅነቱ ፡ (ምሥጋና ፡ ምሥጋና) (፪x)

ትክክል ፡ ነው ፡ ትክክል ፡ ነው (፮x)