ያዛኝ ፡ ያለህ (Yazagn Yaleh) - ሀና ፡ ተክሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሀና ፡ ተክሌ
(Hana Tekle)

Hana Tekle 2.jpg


(2)

የዘለዓለም ፡ ፈጣሪ
(Yezelalem Fetari)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 6:08
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሀና ፡ ተክሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Hana Tekle)

ማን ፡ ያመልጣል ፡ ከእግዚአብሔር
ማን ፡ ይሸሸጋል ፡ ከጌታ
ቢገለጥ ፡ ታሪካችን
ጉድ ፡ ነው ፡ የእኛ ፡ ገበና
በአደባባይ ፡ ጨዋ ፡ ያረገን
በግል ፡ መክሮ ፡ ያሳፈረን
ዳኝነቱ ፡ ያልተገባን
እኔን ፡ ጨምሮ ፡ ቤቱ ፡ ይቁጠረን

ነግ ፡ በእኔ ፡ ማለት ፡ ጥሩ
በተያዙበት ፡ መያዝ ፡ ሳይያዙ
ጌታን ፡ እንደው ፡ እርሱ ፡ ይምራል
ይህንንም ፡ ይቅር ፡ ይላል (፪x)

ምህረት ፡ የናቀ ፡ ዛሬም ፡ ይፈርዳል
በተማረው ፡ ልክ ፡ ማን ፡ ሰው ፡ ይምራል (፪x)

እንከን ፡ የለሽ ፡ ኑሮ ፡ የለኝም
ታሪኬ ፡ ቢመረመር
ሌላው ፡ ላይ ፡ ስፍረድ ፡ ቆሜ
ወድቆ ፡ እስኪሰበር

የእርሱን ፡ ገሃድ ፡ የእኔ ፡ በቤቴ
ፍርድ ፡ ገምድሎ ፡ የማንነቴ
ብዙ ፡ የተማረ ፡ ብዙ ፡ ይምራል
ነበር ፡ ትምህርቱ ፡ ማን ፡ ግድ ፡ ይለዋል?
አምላክ ፡ አድርጐለት ፡ ሃጥያቱን ፡ ታሪክ
ሰው ፡ አልምር ፡ ብሎት ፡ ሆነ ፡ የዕድሜ ፡ ልክ

አትፍረጅ ፡ አትፍረጅ ፡ ተይ ፡ ነፍሴ
ይፈረድብሻል ፡ አንቺ ፡ ተይ ፡ ምላሴ
እያየሽ ፡ እየኖርሽ ፡ የእርሱን ፡ ምህረት
እንዴት ፡ ግድ ፡ አይልሸም ፡ የሰው ፡ ሕይወት

የማያልፈው ፡ . (1) . ፡ የእራሱን ፡ ቁስለት
አያቆም ፡ መፍረድ ፡ በሰውም ፡ ማንነት
ለከፋ ፡ ቁስል ፡ እንጨት ፡ ይሰዳል
ለታመመ ፡ ሰው ፡ ይህ ፡ መች ፡ ይረዳል

ኧረ ፡ ያዛኝ ፡ ያለህ ፡ ይላል ፡ ጪኸቱ
አላሳልፍ ፡ ቢለው ፡ የሰው ፡ አንደበቱ
በሰው ፡ አፍ ፡ ተመቶ ፡ እያነከሰ
ስንቱ ፡ ተሰብሮ ፡ ከማይሆን ፡ ዋለ ፡ አሃሃ

ማን ፡ ያመልጣል ፡ ከእግዚአብሔር
ማን ፡ ይሸሸጋል ፡ ከጌታ
ቢገለጥ ፡ ታሪካችን
ጉድ ፡ ነው ፡ የእኛ ፡ ገበና
በአደባባይ ፡ ጨዋ ፡ ያረገን
በግል ፡ መክሮ ፡ ያሳፈረን
ዳኝነቱ ፡ ያልተገባን
እኔን ፡ ጨምሮ ፡ ቤቱ ፡ ይቁጠረን

ነግ ፡ በእኔ ፡ ማለት ፡ ጥሩ
በተያዙበት ፡ መያዝ ፡ ሳይያዙ
ጌታን ፡ እንደው ፡ እርሱ ፡ ይምራል
ይህንንም ፡ ይቅር ፡ ይላል (፪x)

ምህረት ፡ የናቀ ፡ ዛሬም ፡ ይፈርዳል
በተማረው ፡ ልክ ፡ ማን ፡ ሰው ፡ ይምራል (፪x)