በጉባኤው ፡ መሃል (Begubaiew Mehal) - ሀና ፡ ተክሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሀና ፡ ተክሌ
(Hana Tekle)

Hana Tekle 2.jpg


(2)

የዘለዓለም ፡ ፈጣሪ
(Yezelalem Fetari)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 4:37
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሀና ፡ ተክሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Hana Tekle)

በጉባኤው ፡ መሃል ፡ በአንድ ፡ አባት ፡ ልጆች ፡ ላይ
የተገፋፋ ፡ ሰው ፡ አንድ ፡ ላይ ፡ ያመልክሃል
አንድ ፡ ላይ ፡ ያመልካል
ውስጡን ፡ እያመመው ፡ ጥላቻው ፡ በርትቶ
ወድሃለው ፡ ይላል ፡ ህዝብህ ፡ ቤትህ ፡ ገብቶ
አንድ ፡ ላይ ፡ ተቀምጦ

ስንበላም ፡ አንድ ፡ ላይ
ስንጠጣም ፡ አንድ ፡ ላይ
ስንገባም ፡ አንድ ፡ ላይ
ስንወጣም ፡ አንድ ፡ ላይ

ይህን ፡ ሁሉ ፡ ዘምን ፡ አንድ ፡ ላይ ፡ ኖረናል
ውስጥ ፡ ውስጡን ፡ ተባልተን ፡ ግን ፡ ተለያይተናል
ምን ፡ ያደርጋል

ፍቅር ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያገናኘን
ፍቅር ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያሰባሰበን
ኢየሱስ ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያገናኘን
ጌታ ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያሰባሰበን

የስስት ፡ ጨርቃችን ፡ መጨረሻው ፡ ብል፡ ነው
ለዛሬ ፡ ያልሆነ ፡ ፍቅራችን ፡ ለመች ፡ ነው
ኧረ ፡ ለማንስ ፡ ነው
ከፍቅሩ ፡ ባለቤት ፡ ከሆነ ፡ ውሎዋችን
በአንድነት ፡ ይገለጥ ፡ እውነት ፡ አምልኳችን
በፍቅር ፡ አምልኳችን

ስንበላም ፡ አንድ ፡ ላይ
ስንጠጣም ፡ አንድ ፡ ላይ
ስንገባም ፡ አንድ ፡ ላይ
ስንወጣም ፡ አንድ ፡ ላይ

ይህን ፡ ሁሉ ፡ ዘምን ፡ አንድ ፡ ላይ ፡ ኖረናል
ውስጥ ፡ ውስጡን ፡ ተባልተን ፡ ተለያይተናል
ምን ፡ ያደርጋል

ፍቅር ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያገናኘን
ፍቅር ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያሰባሰበን
ኢየሱስ ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያገናኘን
ጌታ ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያሰባሰበን

እምነት ፡ ቢሞላ ፡ ዕውቀት ፡ ቢከበኝ
ልሳን ፡ መናገር ፡ ትንቢት ፡ ቢኖረኝ
ሥጋዬን ፡ ለእሳት ፡ ብሰጥ ፡ ፈቅጄ
ባልነፍግ፡ ለድሆች ፡ ያለኝን ፡ ከእጄ [1]
ፍቅር ፡ የሌለው ፡ እልፍ ፡ ደግነት
ጌታ ፡ የሌለበት ፡ መንፈሳዊነት
ወዴት ፡ ወዴት ፡ ነው ፡ ይህ ፡ ከንቱ ፡ ጉዞ
በሃሜት ፡ ታዝሎ ፡ በቂም ፡ ተይዞ
ዞሮ ፡ ለማን ፡ ነው ፡ ይህ ፡ ጥል ፡ ግርግር
አቤል ፡ ከቃየል ፡ የማይሆን ፡ አጥር

ጐራ ፡ ለይቶ ፡ ይቅር ፡ ማድሩ
የእውነት ፡ ፍቅር ፡ ይግባ ፡ መንደሩ
የባላንጣችን ፡ ደስታው ፡ ይደፍርስ
በፍቅር ፡ ዘምተን ፡ ሰላም ፡ እንመልስ
የቁርሾን ፡ ዘመን ፡ ይበቃ ፡ ብለነው
መዘናጠሉ ፡ ነው ፡ ወዲያ ፡ እንጣለው
ፍቅር ፡ ይበቀለው

በረከት ፡ ደርሶ ፡ ደጅ ፡ አይመለስ
የተወሰድው ፡ ክብርም ፡ ይመለስ
ፍቱን ፡ መድሃኒት ፡ ፍቅር ፡ ነው ፡ ፈውሱ
ለምድሪቱ ፡ ቀውስ ፡ ጥያቄ ፡ መልሱ

ፍቅር ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያገናኘን (፪x)
ኢየሱስ ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያገናኘን
ጌታ ፡ አይደለም ፡ ዎይ ፡ ያሰባሰበን

  1. ፩ ቆር ፲፫ ፡ ፩-፫ (1 Cor 13:1-3)