አስደስተዋለሁ (Asdesetewalehu) - ጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ
(Getayawkal and Birucktawit)

Getayawkal and Birucktawit 1.jpg


(1)

ምድር ፡ አለፈላት
(Meder Alefelat)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (2002)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 10:10
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Getayawkal and Birucktawit)

ቤትህ ፡ በምን ፡ ላይ ፡ ነው ፡ የተመሠረተው
ቤትህ ፡ በምን ፡ ላይ ፡ ነው ፡ የተመሠረተው
በአለት ፡ ነው ፡ በአሸዋ ፡ ቤትህ ፡ በምን ፡ ላይ ፡ ነው (፪x)

ቤቴ ፡ አሸዋ ፡ ላይ ፡ ነው ፡ የተመሠረተው
እስከአሁን ፡ ሰላም ፡ ነው ፡ ችግርም ፡ አላየሁ
በጋው ፡ ተስማምቶኛል ፡ ምን ፡ ችግር ፡ ይመጣል
ውኃ ፡ እኮ ፡ በአሸዋ ፡ ወዲያው ፡ ይመጠጣል

"መስሎሃል"

ይልቅ ፡ ወጪ ፡ አታውጡ ፡ አለት ፡ አትቧጥጡ
ወጪን ፡ ይቀንሳል ፡ አሸዋ ፡ እኮ ፡ ሞልቷል
የእኔስ ፡ ቤት ፡ አምራለች ፡ በጣም ፡ ዘንጣለች
ላለሁበት ፡ ጊዜ ፡ ተመችታኛለች

"ተው ፡ ይቅርብህ"

አሸዋ ፡ ከሆነ ፡ የቤትህ ፡ መሠረት (፪x) ፡ አቤት ፡ ጉድ ፡ ፈላበት
አሸዋ ፡ ከሆነ ፡ የቤትህ ፡ መሠረት (፪x) ፡ አቤት ፡ ጉድ ፡ ፈላበት

ክረምት ፡ የመጣ ፡ ቀን ፤ ዝናብ ፡ የመጣ ፡ ቀን
ጐርፉ ፡ የመጣ ፡ ቀን ፤ ንፋስ ፡ የመጣ ፡ ቀን
ጠራርጐ ፡ ይወስደዋል ፡ አንዱንም ፡ ሳያስቀር

ገንዘብህ ፡ ከሆነ ፡ የሕይወትህ ፡ መሠረት
ዕውቀትህ ፡ ከሆነ ፡ የሕይወትህ ፡ መሠረት
አቤት ፡ ጉድ ፡ ፈላበት
ሥልጣንህ ፡ ከሆነ ፡ የሕይወትህ ፡ መሠረት
ጥበብህ ፡ ከሆነ ፡ የሕይወትህ ፡ መሠረት
አቤት ፡ ጉድ ፡ ፈላበት

ችግር ፡ የመጣ ፡ ቀን ፤ ሃዘን ፡ የመጣ ፡ ቀን
መከራ ፡ የመጣ ፡ ቀን ፤ ማጣት ፡ የመጣ ፡ ቀን
ጠራርጐ ፡ ይወስደዋል ፡ አንዱንም ፡ ሳያስቀር

ቤትህ ፡ በምን ፡ ላይ ፡ ነው ፡ የተመሠረተው
ቤትህ ፡ በምን ፡ ላይ ፡ ነው ፡ የተመሠረተው
ባለት ፡ ነው ፡ በአሸዋ ፡ ቤትህ ፡ በምን ፡ ላይ ፡ ነው (፪x)

ቤቴ ፡ በዓለት ፡ ላይ ፡ ነው ፡ የተመሠረተው
ችግሩም ፡ በሽበሽ ፡ ነው ፡ መከራብ ፡ ብዙ ፡ ነው
ጐርፉ ፡ ሲወርድብኝ ፡ ነፋስ ፡ ሲነፍስብኝ
አለት ፡ ላይ ፡ ስላለሁ ፡ ቤቴ ፡ አልፈረሰብኝ

"ኧረ ፡ ምንም ፡ አትሆን"

አለት ፡ በቀላሉ ፡ አይገኝም ፡ ሲሉ
የምደክም ፡ መስሎኝ ፡ ድሮ ፡ ተሞኘሁኝ
የአሸዋ ፡ ነጋዴው ፡ ነበርና ፡ ወሬው
ቤቴን ፡ በዓለት ፡ ብቻ ፡ ሰራሁ ፡ ከነአካቴው

"ደግ ፡ አድርገሃል"

አለቱ ፡ ከሆነ ፡ የቤትህ ፡ መሠረት
አለቱ ፡ ከሆነ ፡ የቤትህ ፡ መሠረት
በቃ ፡ አለፈለት (፪x)

ክረምቱ ፡ ቢመጣ ፤ ዝናቡም ፡ ቢወርድ
ጐርፉ ፡ ቢንደረደር ፤ ንፋሱም ፡ ቢነፍስ
የአንተ ፡ ቤት ፡ እንደሆን ፡ ፈጽሞ ፡ አይላወስ

ኢየሱስ ፡ ከሆነ ፡ የሕይወትህ ፡ መሠረት
ቃሉ ፡ ከሆነልህ ፡ የሕይወትህ ፡ መሠረት
በቃ ፡ አለፈለት (፪x)

መከራ ፡ ቢመጣ ፤ ችግር ፡ ቢደርስብህ
ሃዘን ፡ ቢያጋጥምህ ፤ ማጣት ፡ ቢያስቸግርህ
አትነቃነቅም ፡ አለት ፡ ላይ ፡ ስላለህ

አለቱ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
አለቱ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)

ያየሁት ፡ በስጋ ፡ ዓይን ፡ አይደለም ፡ ግን ፡ እርግጠኛ ፡ ነኝ
በሕይወቴ ፡ አይቼዋለሁ ፡ ፍቅሩ ፡ ሲዳስሰኝ (፬x)

አለቱ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
አለቱ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)

ያየሁት ፡ በስጋ ፡ ዓይን ፡ አይደለም ፡ ግን ፡ እርግጠኛ ፡ ነኝ
በሕይወቴ ፡ አይቼዋለሁ ፡ ፍቅሩ ፡ ሲዳስሰኝ (፬x)

አለቱ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
አለቱ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ መሠረቴ (፬x)