Eyerusalem Negiya/Qen Sale/Awqalehu

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


|ዘማሪ=ኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ |Artist=Eyerusalem Negiya |ርዕስ=አውቃለሁ |Title=Awqalehu |አልበም=ቀን ፡ ሳለ |Album=Qen Sale |Volume=2 |ዓ.ም.=፳ ፻ ፬ |Year=2012 |Track=7 |ቋንቋ=አማርኛ |Language=Amharic

|Lyrics=

 
ግራና ፡ ቀኜን ፡ ከፊት ፡ ከኋላ
ሲጨልምብኝ ፡ ባጣ ፡ ማረፊያ
ተስፋዬ ፡ ያልኩት ፡ በእጄ ፡ ይዤ
ድንገት ፡ ሲከዳኝ ፡ ብቀር ፡ ተክዤ
የተውከኝ ፡ ሲመስለኝ ፡ አምላኬ ፡ ከላይ
ምድር ፡ ጐርብጣ ፡ ቢዘጋ ፡ ሰማይ
አሃሃ ፡ አውቃለሁ

አንተ ፡ ሁልጊዜ ፡ ትክክል ፡ እንደሆንክ
አውቃለሁ ፡ ተናግረህ ፡ ማትፈጽም ፡ ቀላባይ ፡ እንዳልሆንክ

አዝ፦ አውቃለሁ ፡ ለእኔ ፡ መልካም ፡ ሃሳብ ፡ እንዳለህ
ፍቅር ፡ ነው ፡ አላማህ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ውዴ
ፍቅር ፡ ነው ፡ አላማህ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ውዴ (፪x)

ሀጥያቴ ፡ ሲጋለጥ ፡ ለአሉታ ፡ ወሬ
በነበር ፡ ሆኖ ፡ ሳይቀር ፡ ነገሬ
የሽንፈት ፡ ቃላት ፡ ከአፌ ፡ እንዲወጣ
ሲወተውተኝ ፡ ምክንያት ፡ ቢያጣ
ሙሾ ፡ ሲደረድር ፡ ይኸው ፡ ጠፋሁ ፡ ብዬ
በገናዬን ፡ ስጥል ፡ ሊስቅ ፡ ባላንጣዬ
አሃሃ ፡ አውቃለሁ ፡ ዞርበል ፡ አንተ ፡ ክፉ ፡ ብሩህ ፡ ቀን ፡ አያለሁ
አሃሃ ፡ አውቃለሁ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጻዲቅ ፡ ነው ፡ አመሰግናለሁ

አዝ፦ አውቃለሁ ፡ ለእኔ ፡ መልካም ፡ ሃሳብ ፡ እንዳለህ
ፍቅር ፡ ነው ፡ አላማህ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ውዴ
ፍቅር ፡ ነው ፡ አላማህ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ውዴ (፪x)

ልዩ ፡ ነህ
ፍቅር ፡ ነህ
በእኔ ፡ ላይ ፡ አላማህ ፡ ልዩ ፡ ነው
ልዩ ፡ ነው

}}