አታይም ፡ ወደላይ (Atayem Wedelay) - ኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ
(Eyerusalem Negiya)

Eyerusalem Negiya 2.jpg


(2)

ቀን ፡ ሳለ
(Qen Sale)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ ፡ አልበሞች
(Albums by Eyerusalem Negiya)

በኃይለኛው ፡ ላይ ፡ ብርቱ ፡ ኃይለኛ
በሚዳኘው ፡ ላይ ፡ ሲሰየም ፡ ዳኛ
በዓለቃው ፡ ላይ ፡ አለ ፡ አለቃ
የሰው ፡ ሹመቱ ፡ ልኩ ፡ ሲያበቃ

ከፍ ፡ ካሉት ፡ በላይ ፡ ከፍ ፡ ብለህ ፡ በዙፋንህ ፡ ላይ
የከበረ ፡ የታወቀ ፡ የገነነ ፡ ከሁሉ ፡ የላቀ
ከሥም ፡ ሁሉ ፡ ሥመኛ ፡ አንተ ፡ እኮ ፡ ነህ ፡ ዝነኛ
የለህ ፡ አቻ ፡ እኩያ ፡ የለህ ፡ ምትክ ፡ አምሳያ

አዝ፦ አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ አለቃ ፡ ነህ ፡ የሁሉ ፡ ጌታ
አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ ፈጣሪ ፡ ነህ ፡ የሁሉም ፡ መሪ

ከላይ ፡ የመጣው ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ ካለልክ ፡ ከፍ ፡ ያደረገው
እኛ ፡ ዝቅ ፡ ልንል ፡ እርሱ ፡ ግን ፡ ሊልቅ ፡ ነው
የተገባው ፡ ነዉ ፡ ከሁሉ ፡ ሊበልጥ (፪x)

ኧረ ፡ ይህንን ፡ ጌታ
ሊሽር ፡ ማንስ ፡ ሊረታ
ሹመቱ ፡ ዙፋኑ ፡ ጽኑ
ገደብ ፡ የለው ፡ ስልጣኑ

አዝ፦ አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ አለቃ ፡ ነህ ፡ የሁሉ ፡ ጌታ
አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ ፈጣሪ ፡ ነህ ፡ የሁሉ ፡ መሪ

በሃይለኛው ፡ ላይ ፡ ብርቱ ፡ ሃይለእኛ
በሚዳኘው ፡ ላይ ፡ ሲሰየም ፡ ዳኛ
በዓለቃው ፡ ላይ ፡ አለ ፡ አለቃ
የሰው ፡ ሹመቱ ፡ ልኩ ፡ ሲያበቃ

ከፍ ፡ ካሉት ፡ በላይ ፡ ከፍ ፡ ብለህ ፡ በዙፋንህ ፡ ላይ
የከበረ ፡ የታወቀ ፡ የገነነ ፡ ከሁሉ ፡ የላቀ
ከስም ፡ ሁሉ ፡ ስመኛ ፡ አንተ ፡ እኮ ፡ ነህ ፡ ዝነኛ
የለህ ፡ አቻ ፡ እኩያ ፡ የለህ ፡ ምትክ ፡ አምሳያ

አዝ፦ አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ አለቃ ፡ ነህ ፡ የሁሉ ፡ ጌታ
አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ ፈጣሪ ፡ ነህ ፡ የሁሉ ፡ መሪ

በማስተዋል ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ ያለ
እራሱን ፡ አዋርዶ ፡ የከበረ
በሰማይም ፡ በምድርም ፡ ክምድር ፡ በታችም ፡ የገነነ
ምላስ ፡ ሁሉ ፡ ይመሰክራል ፡ ጉልበት ፡ ሁሉ ፡ ይንበረከካል
ለእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ለኢየሱስ ፡ አለቅነት ፡ ተገብቶታል

አዝ፦ አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ አለቃ ፡ ነህ ፡ የሁሉ ፡ ጌታ
አታይም ፡ ወደላይ ፡ የለህም ፡ የበላይ
የሁሉ ፡ ፈጣሪ ፡ ነህ ፡ የሁሉ ፡ መሪ