ማን ፡ ሊሆንልኝ (Man Lihonelegn) - ኤፍሬም ፡ ዳኜ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤፍሬም ፡ ዳኜ
(Ephrem Dagne)

Ephrem Dagne 4.jpg


(4)

አላይም ፡ የኋላ
(Alayem Yehuala)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ (2007)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤፍሬም ፡ ዳኜ ፡ አልበሞች
(Albums by Ephrem Dagne)

አዝ፦ አንደኛ ፡ ነው ፡ብዬ ፡ የምታመንበት (፪x)
በሔድኩበት ፡ ሁሉ ፡ ሁሌ ፡ ሞኮራበት (፪x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ለእኔስ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው (፪x)

ከሲኦል ፡ ደጃፍ ፡ የመለሰኝ (እንደ ፡ ኢየሱሴ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
ለሕይወቴ ፡ ቤዛ ፡ የሆነልኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
እጆቸን ፡ ይዞ ፡ ያሳደገኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
እስከ ፡ ፍጻሜው ፡ የሚያጸናኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ

አዝ፦ አንደኛ ፡ ነው ፡ብዬ ፡ የምታመንበት (፪x)
በሔድኩበት ፡ ሁሉ ፡ ሁሌ ፡ ሞኮራበት (፪x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ለእኔስ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው (፪x)

በሰማይ ፡ ቢሆን ፡ በምድርም (እንደ ፡ ኢየሱሴ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
የልብን ፡ ሃሳብ ፡ የሚረዳኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
በፍቅሩ ፡ ቀርቦ ፡ የሚያጽናናኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
አትድከም ፡ አይዞህ ፡ በርታ ፡ የሚለኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ

አዝ፦ አንደኛ ፡ ነው ፡ብዬ ፡ የምታመንበት (፪x)
በሔድኩበት ፡ ሁሉ ፡ ሁሌ ፡ ሞኮራበት (፪x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ለእኔስ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው (፪x)

ከጠላቶቸ ፡ የታደገኝ (እንደ ፡ ኢየሱሴ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
ስሙን ፡ ስጠራው ፡ አለሁ ፡ የሚለኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
ለቤቱ ፡ ስራ ፡ የመረጠኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ
ታማኝ ፡ አድርጐ ፡ የቆጠረኝ (ለኔ ፡ እንደርሱ ፡ ማን ፡ ሊሆንልኝ

አዝ፦ አንደኛ ፡ ነው ፡ብዬ ፡ የምታመንበት (፪x)
በሔድኩበት ፡ ሁሉ ፡ ሁሌ ፡ ሞኮራበት (፪x)
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ለእኔስ ፡ ኢየሱስ ፡ ነው (፪x)