የአምላኬ (Yeamlakie) - ኤፍሬም አለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤፍሬም አለሙ
(Ephrem Alemu)

Ephrem Alemu 2.png


(2)

ዝናዬ
(Zenayie)

ዓ.ም. (Year): 2009
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤፍሬም አለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Ephrem Alemu)

 
ያምላኬ ፡ ጉዳይ ፡ ከበደብኝ
ቅጥሩ ፡ ፈርሶ ፡ ስላየሁኝ
ልቤን ፡ ላስታመው ፡ ደግሞ ፡ ምግብ ፡ አልበላ
ቅጥሩ ፡ ታድሶ ፡ ካላየሁማ

ኧኸ ፡ ጦቢያው ፡ ሰምበላት
ኧኸ ፡ ውረድ ፡ ሲሉኝ
ቅጥር ፡ ልሰራ ፡ ሄጃለሁኝ (፪x)

ና ፡ ውረድ ፡ ሲሉኝ (፫x)
ስፍራው ፡ ተመችቶኝ ፡ እዛው ፡ ቀረሁኝ
አልወርድም ፡ አልወርድም ፡ ከተራራው ፡ ላይ
የእግዚአብሔርን ፡ ክብር ፡ በዓይኖቼ ፡ እስከማይ

አልዛቤል ፡ ምድሩን ፡ ሃገሩን ፡ ገዝታ
ምን ፡ ሰላም ፡ አለ ፡ ለእኛ ፡ መኝታ
እረፍት ፡ የለኝም ፡ ለሽፋሽፍቴ
እስካያት ፡ ድረስ ፡ ወድቃ ፡ ከፊቴ

ኧኸ ፡ ውሻ ፡ ሲበላት
ኧኸ ፡ በዓይኔ ፡ አያለሁ
የትናገረኝ ፡ ጌታ ፡ ታማኝ ፡ ነው (፪x)

ና ፡ ውረድ ፡ ሲሉኝ (፫x)
ስፍራው ፡ ተመችቶኝ ፡ እዛው ፡ ቀረሁኝ
አልወርድም ፡ አልወርድም ፡ ተራራው ፡ ላይ
የእግዚአብሔርን ፡ ክብር ፡ በዓይኖቼ ፡ እስከማይ

ቤቱ ፡ በሸቀጥ ፡ ነጋዴ ፡ ሞልቶ
አጠራው ፡ ጌታ ፡ ጅራፍን ፡ ሰርቶ
ሁሉም ፡ ይሰግዳል ፡ ለአብ ፡ ክብር
ቤቱ ፡ ሲጠራ ፡ የእግዚአብሔር

ኧኸ ፡ የቤቱ ፡ ቅናት
ኧኸ ፡ እኔን ፡ በልቶኛል
ቤቱ ፡ ሲጠራ ፡ በዓይኔ ፡ ያሳየናል (፪x)