በኔ ፡ ላይ ፡ ልትሰራ (Benie Lay Letsera) - ኤፍሬም ፡ አለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤፍሬም ፡ አለሙ
(Ephrem Alemu)
ርዝመት (Len.): 6:58
ሌሎች ፡ ነጠላ ፡ መዝሙሮች
(Other Singles)
ሌሎች ፡ የኤፍሬም ፡ አለሙ ፡ አልበሞች
(Other Albums ፡ by Ephrem Alemu)

በእኔ ፡ ላይ ፡ ልትሰራ ፡ ጌታ ፡ የወደድከዉ
ምኔ ፡ ደስ ፡ ቢልህ ፡ እንዴት ፡ ብትወደኝ ፡ ነው (፪x)

ምንም ፡ ሳልሰራ ፡ ወደድከኝና
ጌታ ፡ በደምህ ፡ ገዛኸኝና
ከመሬት ፡ ከአፈር ፡ አነሳኸኝ
ሰው ፡ ያላየዉን ፡ አሳየኸኝ

አይገርምም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይገርምም ፡ ወይ
አይደንቅም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይደንቅም ፡ ወይ
በእኔ ፡ በትንሹ ፡ ሲሰራ ፡ መንፈሱ ፡ አሄ

ተራዉ ፡ ሰዉ/ውዳቂው ፡ ከመሬት ፡ ተነስቶ
ሲያመልክህ ፡ እጆቹን ፡ አንስቶን
መንፈስህ ፡ መጥቷል ፡ በጉባኤዉ
የነካዉ ፡ ያመስግነዉ ፡ ዛሬ (፪x)

አይገርምም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይገርምም ፡ ወይ
አይደንቅም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይደንቅም ፡ ወይ
በእኔ ፡ በትንሹ ፡ ሲሰራ ፡ መንፈሱ ፡ አሄ

ከኃጢአቴ ፡ በቀር ፡ አላዉቅም
አንድም ፡ ሚያስመሰግነኝ ፡ የለም
ጌታ ፡ ግን ፡ እጆቹን ፡ ዘርግቶ
ሰራብኝ ፡ አንደበቴን ፡ ከፍቶ (፪x)

አይገርምም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይገርምም ፡ ወይ
አይደንቅም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይደንቅም ፡ ወይ
በእኔ ፡ በትንሹ ፡ ሲሰራ ፡ መንፈሱ ፡ አሄ

የሚሆነዉ ፡ ነገር ፡ ገርሞኛል
ጉባኤዉ ፡ በክብርህ ፡ ተሞልቷል
ዝም ፡ ብዬ ፡ ክብርህን ፡ ሳየዉ
ኦ ፡ እኔ ፡ ማን ፡ ነኝ ፡ በዬ ፡ እላለሁ (፪x)

በእኔ ፡ ላይ ፡ ልትሰራ ፡ ጌታ ፡ የወደድከዉ
ምኔ ፡ ደስ ፡ ቢልህ ፡ እንዴት ፡ ብትወደኝ ፡ ነው (፪x)

ምንም ፡ ሳልሰራ ፡ ወደድከኝና
ጌታ ፡ በደምህ ፡ ገዛኸኝና
ከመሬት ፡ ከአፈር ፡ አነሳኸኝ
ሰው ፡ ያላየዉን ፡ አሳየኸኝ

አይገርምም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይገርምም ፡ ወይ
አይደንቅም ፡ ወይ ፡ ኧረ ፡ አይደንቅም ፡ ወይ
በእኔ ፡ በትንሹ ፡ ሲሰራ ፡ መንፈሱ ፡ አሄ