ቤተ ፡ መንግሥት (Bete Mengist) - እንዳሻው ፡ ታሪኩ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳሻው ፡ ታሪኩ
(Endashaw Tariku)

Endashaw Tariku 1.png


(1)

፩ ፡ መንገድ
(1 Menged)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2014)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 5:49
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳሻው ፡ ታሪኩ ፡ አልበሞች
(Albums by Endashaw Tariku)

ቤተመንግስት ሳለ በረት ተወለድህ
       የነገስታት ንጉስ የባሪያን መልክ ያዝህ
       ባበጀሕው መዳፍ ስቃይ መቀበልህ
       ፈራጅነትን ትተህ ፍርዴን ተሸክመህ ሸንጎ ፊት መቅረብህ
ራስህን ለማዳን አለመሟገትህ
ሁሉን ማድረግ ስትችል እንደማትችል መሆንህ
ለኔ አይደለም ወይ በጦር መወጋትህ
ድልድይ ልትሰራልኝ ደምህን አፈሰስህ
     በመስቀል የምተከው ለኔ ነው ይህን ተረድችያለሁ
     የፈሰሰው ደምህ ማርኮኛል ከምት
      ወደር የሌለው ፍቅርህ ማርኮኛል ከጨለማው መንደር
      የሚያስደንቅ ብርሃን ወጣልኝ በየሱስ ይመስገን እግዚአብሄር(አባ ስሙ ይክበር)
         የሱስ የሱስ የእግዚአብሄር ልጅ ለዘላለም ስምህ ይክበር
         አምልኮ ይገባሀል አንተ በሰማይ በምድር
         ተመስተን ተመስተን ልበል እኔ ምስጋናን ልዘምር
         ብዙ አለኝ የማወራው የተሰራልኝ ታምር

2.ነውሯን ባደባባይ በገሀድ አውጥተው
  ገበናዋን ገልጠው እጅግ አሸማቀው
ለውግረት ዳኝነት ፈርደው እንድትፈርድባት
ኢያጎሳቆሏት ወዳንተ አመጧት በዲንጋይ ሊወግሯት
 መች እንደፈራችው ዲንጋይ ዘነበባት
  ዳግም አትስሪ ብለህ የምት ፍርድን ሽረህ በነጻ ለቀካት
ስለምህረትህ እኔም አለኝ ምለው
ከመሞት መዳኔ ጌታ ሆይ ባንተ ነው
            በመስቀል የምተከው ለኔ ነው ይህን ተረድችያለሁ
     የፈሰሰው ደምህ ማርኮኛል ከምት
      ወደር የሌለው ፍቅርህ ማርኮኛል ከጨለማው መንደር
      የሚያስደንቅ ብርሃን ወጣልኝ በየሱስ ይመስገን እግዚአብሄር(አባ ስሙ ይክበር)
         የሱስ የሱስ የእግዚአብሄር ልጅ ለዘላለም ስምህ ይክበር
         አምልኮ ይገባሀል አንተ በሰማይ በምድር
         ተመስተን ተመስተን ልበል እኔ ምስጋናን ልዘምር
         ብዙ አለኝ የማወራው የተሰራልኝ ታምር