ፍቅርህ ፡ መልካም ፡ ነው (Feqreh Melkam New) - እንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ
(Endalkachew Hawaz)

Endalkachew Hawaz 3.jpg


(3)

እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነው
(Egziabhier Teleq New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳልካቸው ፡ ሃዋዝ ፡ አልበሞች
(Albums by Endalkachew Hawaz)

 
ከወይን ፡ ጠጅ ፡ ይልቅ ፡ ፍቅርህ ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ለእኔ (፪x)
አመልክሃለሁ ፡ በቀንም ፡ በሌሊትም ፡ ኢየሱስ ፡ መድህኔ (፪x)

የህይወቴ ፡ ጌታ ፡ የሕይወቴ ፡ ንጉሥ
አንተ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ
የሕይወቴ ፡ ተስፋ ፡ የመኖሬ ፡ ትርጉም
ከአንተ ፡ ውጬ ፡ ሌላ ፡ የለም ፡ አዎ ፡ ሌላ ፡ የለም
አንተ ፡ ብቻ ፡ ነህ ፡ ለዘለዓለም ፡ አዎ ፡ ለዘለዓለም (፪x)

እስከዛሬ ፡ ስኖር ፡ በዚህች ፡ ምድር
አንድም ፡ አላየሁም ፡ ከአንተ ፡ በቀር
(፪x)
ሁሉ ፡ ሲይዙት ፡ ባዶ ፡ ነው ፡ ሲጨብጡት ፡ እንደ ፡ ጉም ፡ ነው
ኢየሱስ/ጌታ ፡ በአንተ ፡ ማረፍ ፡ ግን ፡ እጅግ ፡ መታደል ፡ ነው (፪x)

እገባለሁ ፡ ወደውስጥ ፡ አንተ ፡ ወዳለህበት
እመጣለሁ ፡ በደስታ ፡ ለአንተ ፡ ልገዛ ፡ ጌታ
እገባለሁ ፡ ወደውስጥ ፡ አንተ ፡ ወዳለህበት (ወዳለህበት)
እመጣለሁ ፡ በደስታ ፡ ለአንተ ፡ ልገዛ ፡ ጌታ (እየሰገድኩ)

እየሰገድኩ ፡ እያመለኩ ፡ አንተን ፡ አከብራለሁ
እየሰገድኩ ፡ እያመለኩ ፡ (ለአንተ ፡ እገዛለሁ) ለአንተ ፡ እገዛለሁ
እየሰገድኩ (እየሰገድኩ) ፡ እያመለኩ ፡ (አንተን ፡ አነግሳለሁ) አንተን ፡ አነግሳለሁ
እየሰገድኩ (ጌታዬ) ፡ እያመለኩ (ለአንተ ፡ እኖራለሁ) ፡ ለአንተ ፡ እኖራለሁ
እየሰገድኩ ፡ እያመለኩ ፡ (አንተን ፡ አንተን) አንተን ፡ አከብራለሁ
እየሰገድኩ ፡ እያመለኩ ፡ (ለአንተ ፡ እገዛለሁ) ለአንተ ፡ እገዛለሁ
እየሰገድኩ (እየሰገድኩ) ፡ እያመለኩ ፡ (ጌታ ፡ አነግሻለሁ) አንተን ፡ አነግሳለሁ
እየሰገድኩ ፡ እያመለኩ ፡ ለአንተ ፡ እኖራለሁ