ድንቅ ፡ ነህ (Denq Neh) - እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
Broom.png ይህ ፡ ጽሑፍ ፡ ገና ፡ አልተረጋገጠም ። እርማቶች ፡ ሊያስፈልጉት ፡ ይችላል ። ከቻሉ ፡ እርስዎ ፡ ያሻሽሉት
እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ
(Endale Woldegiorgis)

Endale Woldegiorgis 5.jpg


(5)

ዘላለማዊ
(Zelalemawi)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፲ (2018)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:47
ጸሐፊ (Writer): ዮአኪን ፡ ብርሃኑ
(Yoakin Berhanu
Property "Writer" has been marked for restricted use.
)
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ ፡ አልበሞች
(Albums by Endale Woldegiorgis)

ጌታ ፡ ፈጣሪዬ ፡ ስለ ፡ አፈጣጠሬ
ስለሚያስደንቀው ፡ ስለ ፡ አካል ፡ ክፍሌ

  ላመሰግንህ ፡ እፈልጋለው
  ግሩም ፡ ድንቅ ፡ ሆኜ ፡ ተፈጥሪያለው [፪X]

    ግሩም ፡ ነህ ፡ የሰራሀኝ
    ድንቅ ፡ ነህ ፡ የፈጠርከኝ [፪X]

የማመስገኛ ፡ ምክንያት ፡ ከሆነ
ከቁጥር ፡ በላይ ፡ እኔ ፡ ጋር ፡ አለ
እግሬ ፡ ሲራመድ ፡ ሚዛን ፡ ጠብቆ
ዓይኔም ፡ ሲያይልኝ ፡ ቅርብም ፡ አርቆ
በራስ ፡ ቅሌ ፡ ላይ ፡ ሲበቅል ፡ ፀጉሬ
ጣቶቼ ፡ ላይ ፡ ሲያድግ ፡ ጥፍሬ
ውበት ፡ አላቸው ፡ በየቦታቸው
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ የሰራሃቸው [፪X]

    ግሩም ፡ ነህ ፡ የሰራሀኝ
    ድንቅ ፡ ነህ ፡ የፈጠርከኝ [፪X]

ሰው ፡ ሰውን ፡ ቢሰራው
ቢያበጀው ፡ እስትንፋስ ፡ ቢሰጠው
የሚከፍለው ፡ አጥቶ
ሁሉም ፡ ሰው ፡ መኖር ፡ በተሳነው

ይተመን ፡ ቢባል ፡ በዋጋ ፡ የአካል ፡ ክፍሌ
በዓለም ፡ ያለው ፡ ሃብት ፡ በሙሉ ፡ አይመጥን ፡ ለኔ
እንዃን ፡ ሁሉንም ፡ ይቅርና ፡ አንዱንስ ፡ እንኳ
መፍጠር ፡ ያልቻለው ፡ የሰው ፡ ልጅ ፡ እንዴት ፡ ይመካ

    ግሩም ፡ ነህ ፡ የሰራሀኝ
    ድንቅ ፡ ነህ ፡ የፈጠርከኝ [፪X]

በሚጥም ፡ ዜማ ፡ የሚያዜመው ፡ የአንተን ፡ ዝማሬ
ገንዘብ ፡ ሊገዛው ፡ አይችል ፡ ይህ ፡ አንደበቴ [፪X]

ጌታ ፡ ፈጣሪዬ ፡ ስለ ፡ አፈጣጠሬ
ስለሚያስደንቀው ፡ ስለ ፡ አካል ፡ ክፍሌ

 ላመሰግንህ ፡ እፈልጋለው
 ግሩም ፡ ድንቅ ፡ ሆኜ ፡ ተፈጥሪያለው [፪X]

    ግሩም ፡ ነህ ፡ የሰራሀኝ
    ድንቅ ፡ ነህ ፡ የፈጠርከኝ [፪X]