የወንጌል ፡ አርበኛ (Yewengiel Arbegna) - እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ
(Endale Woldegiorgis)

Endale Woldegiorgis 1.jpg


(1)

የወንጌል ፡ አርበኛ
(Yewengiel Arbegna)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 4:47
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ ፡ አልበሞች
(Albums by Endale Woldegiorgis)

አዝአርበኛ ፡ ነኝ (፪x) ፡ የወንጌል ፡ አርበኛ
ጌታም ፡ አድርጐኛል ፡ የእውነት ፡ ሰራተኛ (፪x)

አልፈራ ፡ አልደነግጥ ፡ ልቤም ፡ አይሸበር
ጌታ ፡ ፍርሃቴን ፡ አድርጐታል ፡ ሰበር (አድርጐታል ፡ ሰበር)
ጉልበታም ፡ መንፈሱ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ተለቋል
ጠላቴ ፡ ይህን ፡ አይቶ ፡ ሁሌ ፡ ያንዣብባል

ይዙር ፡ ያንዣብ ፡ እንጂ ፡ ምኔን ፡ ያገኘዋል
(ይዙር ፡ ያንዣብ ፡ እንጂ ፡ ምኔን ፡ ያገኘዋል)
እኔን ፡ ሊነካ ፡ ሲል ፡ እሳት ፡ ይቀድመዋል (፪x)

አዝአርበኛ ፡ ነኝ (፪x) ፡ የወንጌል ፡ አርበኛ
ጌታም ፡ አድርጐኛል ፡ የእውነት ፡ ሰራተኛ (፪x)

ቅጥሬ ፡ የእግዚአብሔር ፡ ጦር ፡ ደሞዜ ፡ በሰማይ
ይሄ ፡ ስለሆነ ፡ ምንም ፡ ምንም ፡ አላይ (ምንም ፡ ምንም ፡ አላይ)
በሃይል ፡ ተሞልቼ ፡ በብርቱ ፡ እዋጋለሁ
ያዘዘኝን ፡ ጌታ ፡ ደስ ፡ ደስ ፡ ላሰኘው

አዝአርበኛ ፡ ነኝ (፪x) ፡ የወንጌል ፡ አርበኛ
ጌታም ፡ አድርጐኛል ፡ የእውነት ፡ ሰራተኛ (፪x)

በጠቅላዩ ፡ ገዤ ፡ በኢየሱስ ፡ ታዝዤ
ወደጠላት ፡ መንደር ፡ በመንፈስ ፡ ገስግሼ (በመንፈስ ፡ ገስግሼ)
ጉድ ፡ ሳልሰራ ፡ አልመጣም ፡ በፍፁም ፡ በባዶ
አየዋለሁ ፡ ጠላት ፡ በእሳት ፡ ቆስሎ ፡ ነዶ

ይዙር ፡ ያንዣብ ፡ እንጂ ፡ ምኔን ፡ ያገኘዋል
(ይዙር ፡ ያንዣብ ፡ እንጂ ፡ ምኔን ፡ ያገኘዋል)
እኔን ፡ ሊነካ ፡ ሲል ፡ እሳት ፡ ይቀድመዋል (፪x)

ደግሞ ፡ ለጠላቴ ፡ እድል ፡ ፈንታ ፡ አልሰጥም
ከደሊላ ፡ ጭን ፡ ላይ ፡ ተኝቼ ፡ አልገኝም (አልገኝም)
የጌታዬ ፡ መንፈስ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ ስላለ
እንደወደደው ፡ ያድርገኝ ፡ እርሱ ፡ እንደፈለገ

አዝአርበኛ ፡ ነኝ (፪x) ፡ የወንጌል ፡ አርበኛ
ጌታም ፡ አድርጐኛል ፡ የእውነት ፡ ሰራተኛ (፪x)