ይነጋል (Yenegal) - እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
እንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ
(Endale Woldegiorgis)

Endale Woldegiorgis 1.jpg


(1)

የወንጌል ፡ አርበኛ
(Yewengiel Arbegna)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:38
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የእንዳለ ፡ ወልደጊዮርጊስ ፡ አልበሞች
(Albums by Endale Woldegiorgis)

አዝ፦ መልካም ፡ እረኛዬ ፡ ኢየሱስ
ምሥጋናዬ ፡ ይሄው (፪x)
አንተ ፡ ስላለኸኝ ፡ ለምን ፡ እሰጋለሁ
ይነጋል ፡ እላለሁ ፣ ይነጋል

በጊዜው ፡ ነገር ፡ ላይ ፡ ዐይኖቼን ፡ አልጥልም
ቀኑ ፡ በሎ??? ፡ እዛ ፡ ላይ ፡ እንደመሸ ፡ አይቀርም
የገባችው ፡ ፀሐይ ፡ መውጣቷ ፡ ለማይቀር
ዝምብዬ ፡ ላመስግን ፡ ሌቱን ፡ ሳልሻገር

አዝ፦ መልካም ፡ እረኛዬ ፡ ኢየሱስ
ምሥጋናዬ ፡ ይሄው (፪x)
አንተ ፡ ስላለኸኝ ፡ ለምን ፡ እሰጋለሁ
ይነጋል ፡ እላለሁ ፣ ይነጋል

አይደለሁም ፡ አይደለሁም ፡ ብቸኛ
አብሮኝ ፡ ሚሄድ ፡ አለ
አይዞህ ፡ አይዞህ ፡ የሚል
በርታ ፡ ትደርሳለህ (፪x)

በከበረ ፡ አሰራር ፡ ቤቱን ፡ ሰሮቶናል
በፀጋው ፡ ስጦታ ፡ ውስጤን ፡ ሞልቶታል
የክብሩን ፡ ቤት ፡ እርሱ ፡ ማክበር ፡ ስለሚያውቅ
ይኑርብኝ ፡ እንጂ ፡ ለምን ፡ ልጨነቅ

ወጀቡ ፡ ቢበዛም ፡ መልካም ፡ እያየሁ ፡ ነው
በዶት ፡ የተኛ ፡ ይህን ፡ ከየት ፡ አገኘው
ጌታ ፡ ተገልጦልኝ ፡ ብዙ ፡ ተምሬያለሁ
ብኞአል ፡ ያልኩህ ፡ ሁሉ ፡ ፈጽማለሁ

አይደለሁም ፡ አይደለሁም ፡ ብቸኛ
አብሮኝ ፡ ሚሄድ ፡ አለ
አይዞህ ፡ አይዞህ ፡ የሚል
በርታ ፡ ትደርሳለህ (፪x)

አዝ፦ መልካም ፡ እረኛዬ ፡ ኢየሱስ
ምሥጋናዬ ፡ ይሄው (፪x)
አንተ ፡ ስላለኸኝ ፡ ለምን ፡ እሰጋለሁ
ይነጋል ፡ እላለሁ ፣ ይነጋል