ተመስገን (Temesgen) - ኤልያስ ፡ አብጤ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤልያስ ፡ አብጤ
(Elias Abte)

Lyrics.jpg


(1)

የሚጤስ ፡ ጧፌን ፡ አላጠፋም
(Yemitesewen Tuafen Alatefam)

ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤልያስ ፡ አብጤ ፡ አልበሞች
(Albums by Elias Abte)

ተመስገን ተመስገን ተመስገን
ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በሰማይ ተመስገን በምድር ተመስገን
ማን አለኝ ከአንተ ሌላ
የህይወቴ ከለላ
ማን አለኝ ከአንተ ወዲያ
ተመስገን ሃሌሉያ

በህይወቴ የሞላው የሃጥያት ነቀርሳ
ለሞት እስኪያስጨንቅ እጅጉን ሲበዛ
የጣር ጩኸቴን ሰምቶ ከሰማይ ወረደ
ነፍሴን ሰላም ሰጣት ሞቴን አስወገደ
የማይገባኝን ሰማያዊ ጥሪ
የጠራኝ ሳያንሰው አረገኝ መስካሪ
የምህረቱን ብዛት በነፍሴ አሳየኝ
በህይወት ስላኖረኝ ክብርን እሰዋለሁኝ

ተመስገን ተመስገን ተመስገን
ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በሰማይ ተመስገን በምድር ተመስገን
ማን አለኝ ከአንተ ሌላ
የህይወቴ ከለላ
ማን አለኝ ከአንተ ወዲያ
ተባረክ ሃሌሉያ

በበረታ ሃዘን መንፈሴ ተሰብሮ
መጽናናት ሲርቀኝ ዘመናትን ቆጥሮ
በድካም በዝለት በወደኩት ስፍራ
ውዴ ኢየሱስ መጣ በስሜ ተጣራ
እንባዬን አበሰ አይኖቼን ከፈተ
ለደቀቀው ልቤ መጽናናትን ሰጠ
እንደርሱ ሚሆነኝ አላገኘሁምና
በፊቱ እሰዋለሁ ለስሙ ምስጋና

ተመስገን ተመስገን ተመስገን
ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በሰማይ ተመስገን በምድር ተመስገን
ማን አለኝ ከአንተ ሌላ
የህይወቴ ከለላ
ማን አለኝ ከአንተ ወዲያ
ተባረክ ሃሌሉያ

ቁስሌን በዘይት ስታሽ ድርቀቴን ስትፈውስ
ስብራቴን ስትጠግን አንባዬን ስታብስ
ጠያቂዎቼ ብዙ አስታማሚዎቼ
ከኔ እንደማይሻሉ አየሁኝ በአይኖቼ
መጽናናት ሃይልንም ከእኔ ጠበቁ
ከአፌ በወጣው ቃል ተፈውሰው ሳቁ
ክብሬም ታድሶልኝ በትሬም ለምልሞ
ደስታዬን ለማየት ሰዉ ተሽቀዳድሞ

ተመስገን ተመስገን ተመስገን
ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በሰማይ ተመስገን በምድር ተመስገን
ማን አለኝ ከአንተ ሌላ
የህይወቴ ከለላ
ማን አለኝ ከአንተ ወዲያ
ተባረክ ሃሌሉያ

ብላቴናነቴ ተንቆ ወንጭፌ
ከጎልያድ አንደበት እርግማን ጠግቤ
ቅናቱ ሲበላኝ የስምህ መሰደብ
ፈተና ሆኖ ፊቴ በእንባ ሲታጠብ
በእኔ ላይ የአለው የመንፈስህ ብርታት
በክቡር ስምህ ስልጣን ጉልበትህ ሲገለጥ
ያነሳሁት ድንጋይ መቼ የዋዛ ሆነ
ጠላቴን አድቅቆ ስምህን አስከበረ

ተመስገን ተመስገን ተመስገን
ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በሰማይ ተመስገን በምድር ተመስገን
ማን አለኝ ከአንተ ሌላ
የህይወቴ ከለላ
ማን አለኝ ከአንተ ወዲያ
ተባረክ ሃሌሉያ
ማን አለኝ ከአንተ ወዲያ
ተመስገን ሃሌሉያ