ጋርዳቸው ፡ ከመታከት (Gardachew Kemetaket) - ደረጀ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ደረጀ ፡ ከበደ
(Dereje Kebede)

Dereje Kebede 6.png


(6)

ዝም ፡ አልልም
(Zem Alelem)

ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Dereje Kebede)

ለረጅም ፡ ዘመናት ፡ ተቆልፎባቸው ፡ ኤሄሄ ፡ ኤሄሄ ፡ ኤሄዉ
የፈርዖን ፡ ሠራዊት ፡ የሚያንገላታቸው
አሉ ፡ የተገፉ ፡ ስምህን ፡ ለማስከበር ፡ ኤሄሄ ፡ ኤሄሄ ፡ ኤሄዉ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ገርስሰው ፡ የጠላትን ፡ መንደር (፪x)

አዝ፦ ስለ ፡ ሥምህ ፡ ተጠልተው ፡ ያሉትን ፡ በሰንሰለት (፪x)
አብራላቸው ፡ ክብርህን ፡ ጋርዳቸው ፡ ከመታከት
ግንባራቸው ፡ ይጠንክር ፡ ጠላታቸው ፡ ይርበትበት
ለሥምህ ፡ ነዉና ፡ ልጆችህን ፡ አጽና

አንተን ፡ እንዲክዱ ፡ ባንተ ፡ እንዲያማርሩ ፡ ኡሁሁ ፡ ኡሁሁ ፡ ኡሁዉ
ይሸርባል ፡ ጠላት ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ ምስጢሩ
ምሬት ፡ በሕይወታቸው ፡ እንዳይሆን ፡ ጋርዳቸው ፡ ኤሄሄ ፡ ኤሄሄ ፡ ኤሄው
ፈቃድህ ፡ ይፈፀም ፡ እንድትከብርባቸው (፪x)

አዝ፦ ስለ ፡ ሥምህ ፡ ተጠልተው ፡ ያሉትን ፡ በሰንሰለት (፪x)
አብራላቸው ፡ ክብርህን ፡ ጋርዳቸው ፡ ከመታከት
ግንባራቸው ፡ ይጠንክር ፡ ጠላታቸው ፡ ይርበትበት
ለሥምህ ፡ ነዉና ፡ ልጆችህን ፡ አጽና

ጠላትም ፡ ይንቀጥቀጥ ፡ ይታሰር ፡ ምላሱ ፡ ኡሁሁ ፡ ኡሁሁ ፡ ኡሁዉ
ይተብተብ ፡ እጅ ፡ እግሩ ፡ ይቅር ፡ መላወሱ
ፍጥረት ፡ ሁሉ ፡ ይመስክር ፡ ስለ ፡ ኃያልነትህ ፡ እሂሂ ፡ እሂሂ ፡ እሂ
ይሳቁ ፡ በፈርዖን ፡ ድል ፡ ያርጉ ፡ ልጆችህ (፪x)

አዝ፦ ስለ ፡ ሥምህ ፡ ተጠልተው ፡ ያሉትን ፡ በሰንሰለት (፪x)
አብራላቸው ፡ ክብርህን ፡ ጋርዳቸው ፡ ከመታከት
ግንባራቸው ፡ ይጠንክር ፡ ጠላታቸው ፡ ይርበትበት
ለሥምህ ፡ ነዉና ፡ ልጆችህን ፡ አጽና

ከእንግዲህ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ፀሎታችን ፡ ስማ ፡ አሀሀ ፡ አሀሀ ፡ አሀ
ታምነናል ፡ በኃይልህ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ አንተማ
እንክትክት ፡ ብለዉ ፡ የወህኒ ፡ መዝጊያዎች ፡ ኦሆሆ ፡ ኦሆሆ ፡ ኦሆች
ያመልኩሃል ፡ በክብር ፡ በድል ፡ ያንተ ፡ ልጆችህ (፪x)

አዝ፦ ስለ ፡ ሥምህ ፡ ተጠልተው ፡ ያሉትን ፡ በሰንሰለት (፪x)
አብራላቸው ፡ ክብርህን ፡ ጋርዳቸው ፡ ከመታከት
ግንባራቸው ፡ ይጠንክር ፡ ጠላታቸው ፡ ይርበትበት
ለሥምህ ፡ ነዉና ፡ ልጆችህን ፡ አጽና (፪x)