የአድናቆት ፡ ቀን (Yeadnaqot Qen) - ደረጀ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ደረጀ ፡ ከበደ
(Dereje Kebede)

Dereje Kebede 9.jpg


(9)

የአድናቆት ፡ ቀን ፡ ለእግዚአብሔር
(Yeadnaqot Qen LeEgziabhier)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Dereje Kebede)

የአድናቆት ፡ ቀን ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ለወደደን
የሚገባው ፡ እርሱ ፡ ነው ፡ እውነቱን ፡ እንወቅ ፡ ጠንቅቀን
ጀብዱው ፡ ገድሉ ፡ የሚወራለት
ጭፍራ ፡ አለቃው ፡ የሚስግዱለት
እግዚአብሔር ፡ ምሥጉን ፡ ሥም ፡ ያለው
አድናቆቱም ፡ ምሥጋናውም ፡ መገረሙም ፡ ለእርሱ ፡ ሥም ፡ ነው

ማነው ፡ ፍጥረትን ፡ የሰራ ፡ ሰማይ ፡ ምድርን ፡ የቀየሰው
ማነው ፡ በአፍንጫው ፡ እፍ ፡ ያለ ፡ የሕይወትን ፡ እስትንፋስ ፡ ለሰው
ማነው ፡ ነፋስን ፡ አንፋሹ ፡ የእሳት ፡ የውሃው ፡ አለቃ
ማነው ፡ አዛዥ ፡ የጸሀይዋ ፡ ማነው ፡ አዛዥ ፡ የጨረቃ

ማነው ፡ የምድርን ፡ ዳርቻ ፡ በእጆቹ ፡ መዳፍ ፡ ያኖረ
ማነ ፡ ፈርዖንን ፡ በዝቅጠት ፡ በውኃ ፡ በታች ፡ ያስቀረ
ማነው ፡ ከፍታን ፡ የሚያዘው ፡ ዝቅታም ፡ የሚያረግድለት
ማነው ፡ ብድራትን ፡ መላሽ ፡ ከቅርብ ፡ ወይም ፡ ከርቀት

እግዚአብሔር (፬x)
ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ እግዚአብሔር
አንተ ፡ ብቻ ፡ አንተ ፡ ክብር (፫x)

አለቆች ፡ የምድር ፡ ፈርጆች ፡ ጐልማሶች ፡ ቆነጃጅቶች
እሳትና ፡ በረዶ ፡ አመዳይ ፡ ጨምሮም ፡ ውርጮች
ተራሮችና ፡ ኮረብቶች ፡ ፍሬ ፡ የሚያፈሩ ፡ ዝግቦች
በቃሉ ፡ ሲንቀጠቀጡ ፡ እዩት ፡ ሲያደንቁት ፡ ፍጥረቶች

ማነው ፡ የዋሁን ፡ ታዳጊ ፡ መመኪያ ፡ ለቅዱሳኑ
ማነው ፡ ቅን ፡ ፈራጅ ፡ መጠጊያ ፡ ለሥሙ ፡ ታምነው ፡ ለጸኑ
ማነው፡ ጉሙን ፡ የሚበትን ፡ የአንበሳን ፡ መንጋጋ ፡ ያደቀቀ
ማነው ፡ ወጥመድን ፡ ሰባሪ ፡ ህዝቡን ፡ ከግዞት ፡ የጠበቀ

እግዚአብሔር (፬x)
ቅዱስ ፡ ቅዱስ ፡ እግዚአብሔር
አንተ ፡ ብቻ ፡ አንተ ፡ ክብር (፫x)