ትህትና ፡ ሊያስተምረኝ (Tehetena Liyastemregn) - ደረጀ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ደረጀ ፡ ከበደ
(Dereje Kebede)

Lyrics.jpg


(4)

መንግሥተ ፡ ሰማይ
(Mengeste Semay)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፸ ፪ (1980)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 3:53
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Dereje Kebede)

አዝ፦ ትህትና ፡ ሊያስተምረኝ ፡ ወዶ
እግር ፡ አጠበ ፡ ባርያውን ፡ ወርዶ
እራሱን ፡ አዋርዶ (፪x)

ደቀ ፡ መዛሙርቱ ፡ አግራቸው ፡ ቆሸሸ
አደፈ ፡ ጐደፈ ፡ ፍፁም ፡ ተበላሸ
ሁሉን ፡ የፈጠረ ፡ ሰውን ፡ የወደደ
ጭቃውን ፡ ሊያስወግድ ፡ ወደታች ፡ ወረደ

አዝ፦ ትህትና ፡ ሊያስተምረኝ ፡ ወዶ
እግር ፡ አጠበ ፡ ባርያውን ፡ ወርዶ
እራሱን ፡ አዋርዶ (፪x)

እርሱ ፡ ያላጠበው ፡ ከእርሱ ፡ ጋር ፡ አይኖርም
አይቆርስም ፡ ከአምላክ ፡ ጋራ ፡ አንድነት ፡ የለውም
ጴጥሮስ ፡ ይህን ፡ አይቶ ፡ ሰውነቴን ፡ ደግሞ
እጠበኝ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ አለውም ፡ ተማጽኖ

አዝ፦ ትህትና ፡ ሊያስተምረኝ ፡ ወዶ
እግር ፡ አጠበ ፡ ባርያውን ፡ ወርዶ
እራሱን ፡ አዋርዶ (፪x)

በሚደነቅ ፡ ብርሃን ፡ የሚኖር ፡ ፈጣሪ
አልፋና ፡ ኦሜጋ ፡ የፍጥረታት ፡ ሰሪ
ማበሻ ፡ ጨርቅ ፡ ወስዶ ፡ እግር ፡ ሊያጥብ ፡ ወረደ
ዝቅ ፡ አደረገ ፡ እራሱን ፡ ለሰው ፡ አዋረደ

አዝ፦ ትህትና ፡ ሊያስተምረኝ ፡ ወዶ
እግር ፡ አጠበ ፡ ባርያውን ፡ ወርዶ
እራሱን ፡ አዋርዶ (፪x)

የሁሉ ፡ ማሰሪያ ፡ አላማ ፡ ያለው ፡ ነው
ጌታ ፡ ይህን ፡ አድርጓል ፡ እኔስ ፡ እንደምነው
የወንድሜን ፡ እግር ፡ እስካጥብ ፡ ዝልቅ ፡ ካልኩ
እውነትም ፡ ኢየሱስን ፡ በእርግጥ ፡ ተከተልኩ

አዝ፦ ትህትና ፡ ሊያስተምረኝ ፡ ወዶ
እግር ፡ አጠበ ፡ ባርያውን ፡ ወርዶ
እራሱን ፡ አዋርዶ (፪x)

ባሪያ ፡ ከሚያኖረው ፡ አይበልጥም ፡ አላቸው
መልዕክተኛም ፡ አይበጅ ፡ ይልቁን ፡ ከላከው
እንግዲህ ፡ ጌታችሁ ፡ እኔ ፡ ይህን ፡ ስፈጽም
አድርጉት ፡ ለሁሉም ፡ ዛሬ ፡ ሁኑ ፡ እናንተም

አዝ፦ ትህትና ፡ ሊያስተምረኝ ፡ ወዶ
እግር ፡ አጠበ ፡ ባርያውን ፡ ወርዶ
እራሱን ፡ አዋርዶ (፪x)