አልተማረም ፡ አሉኝ (Altemarem Alugn) - ደረጀ ፡ ከበደ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ደረጀ ፡ ከበደ
(Dereje Kebede)

Lyrics.jpg


(Volume)

ስብስብ
(Collection 2)

ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 5:47
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የደረጀ ፡ ከበደ ፡ አልበሞች
(Albums by Dereje Kebede)

የማመልከው ፡ አምላክ ፡ ሳይንስ ፡ አይጨብጠው
የእብድ ፡ ቃላት ፡ ብዛት ፡ በእውነት ፡ አይገምተው
መስፈሳዊ ፡ አይኖች ፡ ተከፍተው ፡ ካላዩት
ቃሉ፡ ሞኝነት ፡ ነው ፡ አውቀናል ፡ ለሚሉት

አዝ፦ ሞኝ ፡ ነው ፡ አልተማረም ፡ አሉኝ
ለእግዚአብሔር ፡ አድሬለት ፡ ቢያዩኝ
ትርፌን ፡ እና ፡ ጥቅሜን ፡ ባለማወቃቸው
እኔ ፡ አዘንኩላቸው (፪x)

ይልቅስ ፡ ሳይጨልም ፡ መዝጊያው ፡ ሳይቆለፍ
የሰው ፡ ልጅ ፡ ይመለስ
ለሚጠፋው ፡ አለም ፡ ጉልበቱን ፡ ከማፍሰስ (፪x)

የሚጠፋ ፡ ጥሪት ፡ ማከማቸት ፡ ትቼ
ዘላለማዊውን ፡ ለማግኘት ፡ ዘይጄ
ጌታዬን ፡ የሙጥኝ ፡ ብዬ ፡ መወሰኔ
ከአዋቂዎች ፡ በላይ ፡ አልሆንኩም ፡ ወይ ፡ እኔ

አዝ፦ ሞኝ ፡ ነው ፡ አልተማረም ፡ አሉኝ
ለእግዚአብሔር ፡ አድሬለት ፡ ቢያዩኝ
ትርፌን ፡ እና ፡ ጥቅሜን ፡ ባለማወቃቸው
እኔ ፡ አዘንኩላቸው (፪x)

ይልቅስ ፡ ሳይጨልም ፡ መዝጊያው ፡ ሳይቆለፍ
የሰው ፡ ልጅ ፡ ይመለስ
ለሚጠፋው ፡ አለም ፡ ጉልበቱን ፡ ከማፍሰስ (፪x)

ምድር ፡ እና ፡ ሰማይን ፡ ያበጀው ፡ ፈጣሪ
አይመረመርም ፡ ገብቶ ፡ ልብራቶሪ
ቁጥርን ፡ ከቁጥር ፡ ጋር ፡ ሲያጋጩ ፡ ቢኖሩ
አያዩትም ፡ ጌታን ፡ እሩቅ ፡ ነው ፡ ሃገሩ

አዝ፦ ሞኝ ፡ ነው ፡ አልተማረም ፡ አሉኝ
ለእግዚአብሔር ፡ አድሬለት ፡ ቢያዩኝ
ትርፌን ፡ እና ፡ ጥቅሜን ፡ ባለማወቃቸው
እኔ ፡ አዘንኩላቸው (፪x)

ይልቅስ ፡ ሳይጨልም ፡ መዝጊያው ፡ ሳይቆለፍ
የሰው ፡ ልጅ ፡ ይመለስ
ለሚጠፋው ፡ አለም ፡ ጉልበቱን ፡ ከማፍሰስ (፪x)

ሰአቱ ፡ ገና ፡ አለ ፡ ጊዜአችን ፡ አልከፋም
እግዚአብሔር ፡ ደጁን ፡ በሰው ፡ ልጅ ፡ አልዘጋም
ከማንቀላፋቱ ፡ ነቅቶ ፡ ለታረመ
ብርሃን ፡ ነው ፡ ገና ፡ ዛሬ ፡ መች ፡ ጨለመ

አዝ፦ ሞኝ ፡ ነው ፡ አልተማረም ፡ አሉኝ
ለእግዚአብሔር ፡ አድሬለት ፡ ቢያዩኝ
ትርፌን ፡ እና ፡ ጥቅሜን ፡ ባለማወቃቸው
እኔ ፡ አዘንኩላቸው (፪x)

ይልቅስ ፡ ሳይጨልም ፡ መዝጊያው ፡ ሳይቆለፍ
የሰው ፡ ልጅ ፡ ይመለስ
ለሚጠፋው ፡ አለም ፡ ጉልበቱን ፡ ከማፍሰስ (፪x)