መዝሙር ፺፩ (Mezmur 91) - ዳዊት ፡ (ዳኒ) ፡ ወልዴ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ (ዳኒ) ፡ ወልዴ
(Dawit Wolde)

Dawit Wolde 1.jpeg


(1)

መዝሙር ፺ ፩
(Mezmur 91)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ (ዳኒ) ፡ ወልዴ ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Wolde)

"መዝሙር ፡ ፺፩"

“በልዑል ፡ መጠጊያ ፡ የሚኖር
ሁሉንም ፡ በሚችል ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ውስጥ ፡ ያድራል
እግዚአብሔርን ፡ አንተ ፡ መታመኝያዬ ፡ ነህ ፡ እለዋለሁ
አምላኬና ፡ መሸሸጊያዬ ፡ ነው ፡ በእርሱ ፡ እታመናለሁ "

"መዝሙር ፡ ፺፩"

በልዑል ፡ መጠጊያ ፡ የሚኖር
ሁሉንም ፡ በሚችል ፡ አምላክ ፡ ጥላ ፡ ውስጥ ፡ ያድራል
እግዚአብሔርን ፡ አንተ ፡ መታመኛዬ ፡ ነህ ፡ እለዋለሁ
አምላኬና ፡ መሸሸጊያዬ ፡ ነው ፡ በእርሱ ፡ እታመናለሁ (፪x)

አዝ:- ነፍሴን ፡ ከአዳኝ ፡ ወጥመድ ፡ ከአደገኛው ፡ መንገድ
ከለሊቱ ፡ ግርማ ፡ ካስፈሪው ፡ ጨለማ
በቀን ፡ ከሚበረው ፡ ከጠላት ፡ ፍላጻ
በክንፎቹ ፡ ጋርዶ ፡ ሸሽጎኛልና

በእርሱ ፡ እታመናለሁ ፡ ያስጥለኛል
ስሙን ፡ አውቀዋለሁ ፡ ይጋርደኛል
በመከራዬ ፡ ጊዜ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው
ታማኙን ፡ አምላኬን ፡ ላመስግነው

ላመስግነው ፡ ላመስግነው ፡ እርሱ ፡ ታማኝ ፡ ነው (፬x)

አንዳንዴ ፡ እምነቴ ፡ ሲፈተንና ፡ ስታገል
አቋራጭ ፡ መንገድ ፡ ስፈልግ ፡ ቶሎ ፡ ልገላገል
ያን ፡ ጊዜ ፡ ይመጣና ፡ ቅዱስ ፡ ቃሉ ፡ ወደልቤ
ፈጥኖ ፡ ይመልሰኛል ፡ ካልተቀደሰው ፡ ሃሳቤ

አዝ:- ፡ ነፍሴን ፡ ከአዳኝ ፡ ወጥመድ ፡ ከአደገኛው ፡ መንገድ
ከለሊቱ ፡ ግርማ ፡ ካስፈሪው ፡ ጨለማ
በቀን ፡ ከሚበረው ፡ ከጠላት ፡ ፍላጻ
በክንፎቹ ፡ ጋርዶ ፡ ሸሽጎኛልና

በእርሱ ፡ እታመናለሁ ፡ ያስጥለኛል
ስሙን ፡ አውቀዋለሁ ፡ ይጋርደኛል
በመከራዬ ፡ ጊዜ ፡ ከእኔ ፡ ጋር ፡ ነው
ታማኙን ፡ አምላኬን ፡ ላመስግነው (፪x)

ክብር (፱x)

ክብር ለርሱ ፡ ይሁን (፫x) - ክብር ለርሱ ፡ ይሁን (፫x)
ክብር ለርሱ ፡ ይሁን (፫x) - ክብር ለርሱ ፡ ይሁን (፫x)
ክብር ለንጉሡ (፫x) - ክብር ለንጉሡ (፫x)
ክብር ለርሱ ፡ ይሁን (፫x) - ክብር ለርሱ ፡ ይሁን (፫x)
ክብር ለንጉሡ (፫x) - ክብር ለንጉሡ (፫x)