ናፍቃለሁ (Nafeqalehu) - ዳዊት ፡ ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Dawit Getachew 1.jpg


(1)

እጠብቅሃለሁ
(Etebeqehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 5:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ኃያላን ፡ ሲነሱ ፡ እርስ ፡ በዕርሳቸው
ምድር ፡ ስትናወጥ ፡ ግራ ፡ ሲገባቸው
ቀኑ ፡ ሲደርስ ፡ ግን ፡ አንተ ፡ ስትመጣ
ያን ፡ ጊዜ ፡ ያበቃል ፡ የዚች ፡ ዓለም ፡ ጣጣ

አዝ:- ናፍቃለሁ ፡ ያንን ፡ ቀን ፡ ላይ ፡ ሁልጊዜ ፡ እሮጣለሁ
የተሰቀለውን ፡ የሞተውን ፡ የተነሳውን ፡ ላየው
የመላዕክት ፡ ድምፅ ፡ ዝማሬያቸው ፡ ከሩቁ ፡ ይሰማኛል
የምጠብቀው ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መምጫው ፡ ጊዜ ፡ ደርሷል

ሁሉ ፡ በሁሉ ፡ ነው ፡ ምንም ፡ አይጐድለንም
በሰማይ ፡ ቤት ፡ ስቃይ ፡ ጉስቁልና ፡ የለም
እንዘምራለን ፡ ዘለዓለም ፡ በደስታ
ለይሁዳ ፡ አንበሳ ፡ ሞትን ፡ ድል ፡ ለነሳ

አዝ:- ናፍቃለሁ ፡ ያንን ፡ ቀን ፡ ላይ ፡ ሁልጊዜ ፡ እሮጣለሁ
የተሰቀለውን ፡ የሞተውን ፡ የተነሳውን ፡ ላየው
የመላዕክት ፡ ድምፅ ፡ ዝማሬያቸው ፡ ከሩቁ ፡ ይሰማኛል
የምጠብቀው ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ መምጫው ፡ ጊዜ ፡ ደርሷል

ጌታ ፡ ሲመጣ ፡ በመላእክት ፡ ታጅበን
ከሙሽራው ፡ ጋር ፡ ልንኖር ፡ አብረን ፡ እንሄዳለህ
የሚያሰጋን ፡ የለም ፡ ዕዳችን ፡ ሁሉ ፡ ተከፍሏል
በነጽነት ፡ ልንኖር ፡ ከእርሱ ፡ ጋር
ዳግመኛ ፡ በክብር ፡ ይመጣል (፪x)

ጌታ ፡ ሲመጣ ፡ በመላእክት ፡ ታጅበን