ለሥምህ (Lesemeh) - ዳዊት ፡ ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Dawit Getachew 1.jpg


(1)

እጠብቅሃለሁ
(Etebeqehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 5:03
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ትዝ ፡ ይለኛል ፡ የማልረሳው ፡ ብዙ ፡ ታሪክ ፡ አለኝ
ራሴን ፡ አውቃለሁ ፡ ማንነቴን ፡ ከየት ፡ እንዳነሳኝ
ዛሬ ፡ ላይ ፡ ቆሜ ፡ ሳስታውሰው ፡ ያለፈውን ፡ ሁሉ
ስታግዘኝ ፡ ያዩ ፡ ዓይኖቼ ፡ በእንባ ፡ ይሞላሉ

ክብር ፡ ለሥምህ ፡ ይሁን ፡ እዚህ ፡ አደረስከኝ

ቀን ፡ ይመሻል ፡ ደግሞ ፡ ይነጋል
ሁሉም ፡ ነገር ፡ ያልፋል
ትዝታውን ፡ ግን ፡ ለመርሳት ፡ ከቶ ፡ እንዴት ፡ ይቻላል
ባትደርስልኝ ፡ ባትዘረጋው ፡ የምህረት ፡ እጅህን
ሳስበው ፡ እፈራለሁ ፡ መጨረሻዬን

ክብር ፡ ለሥምህ ፡ ይሁን ፡ እዚህ ፡ አደረስከኝ
በደስታ ፡ በሀዘኔ ፡ ከቶ ፡ ሳትለየኝ

ተሸከምከኝ ፡ እዚህ ፡ አደረስከኝ
ቀኖቹ ፡ ቢያልፉ ፡ መቼም ፡ አይረሳኝ

ዛሬ ፡ ቆሜ ፡ ዘምረዋለሁ ፡ ለእኔ ፡ ያደረከው ፡ ብዙ ፡ ነው
አንዳች ፡ የለም ፡ ከእኔ ፡ ነው ፡ የምለው
አመሰግንሃለሁ

ሁሉም ፡ አልፎ ፡ ዛሬ ፡ ቆሜያለሁ
ከአንተ ፡ የተነሳ ፡ እዚህ ፡ አለሁ
ስለነገ ፡ እንዴት ፡ እፈራለሁ
ሕይወቴ ፡ በእጅህ ፡ ነው