ከአድማስ ባሻገር (Keadmas Bashager) - ዳዊት ፡ ጌታቸው

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳዊት ፡ ጌታቸው
(Dawit Getachew)

Dawit Getachew 1.jpg


(1)

እጠብቅሃለሁ
(Etebeqehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 4:58
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳዊት ፡ ጌታቸው ፡ አልበሞች
(Albums by Dawit Getachew)

ከአድማስ ፡ ባሻገር ፡ ከዓይናችን ፡ የራቀ
ከሩቁ ፡ ስናየው ፡ ሰማዩ ፡ ወደቀ
ነገር ፡ ግን ፡ የአራቱም ፡ መጨረሻ ፡ አንተ ፡ ነህ
ፍጥረት ፡ እጅህ ፡ ላይ ፡ ነው ፡ ምን ፡ ያህል ፡ ትልቅ ፡ ነህ

አዝ:- በእውነት ፡ እኛም ፡ አናውቅህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነህ
ከአእምሮአችን ፡ በላይ ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ችሎታህ
ሥራዎችን ፡ ሁሉ ፡ ስለ ፡ አንተ ፡ አወሩ
ይሁን ፡ ስትላቸው ፡ ሆኑ ፡ ፍጥረታት ፡ በሙሉ
ክብር ፡ ለሥምህ ፡ ይሁን

ንፋስ ፡ በምድር ፡ ላይ ፡ እንዴት ፡ ይበተናል
የበረዶው ፡ ክምር ፡ ማን ፡ አጥቦ ፡ አፅድቶታል
ምድርን ፡ ስትሰራ ፡ ማን ፡ ነበረ ፡ አብሮህ
እንዲህ ፡ አድርግ ፡ ብሎህ ፡ ማንስ ፡ አማከረህ

አዝ:- በእውነት ፡ እኛም ፡ አናውቅህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነህ
ከአእምሮአችን ፡ በላይ ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ችሎታህ
ሥራዎችን ፡ ሁሉ ፡ ስለ ፡ አንተ ፡ አወሩ
ይሁን ፡ ስትላቸው ፡ ሆኑ ፡ ፍጥረታት ፡ በሙሉ
ክብር ፡ ለሥምህ ፡ ይሁን

ኪሩቤል ፡ ሱራፌል ፡ የሚያመሰግኑህ
እልፍ ፡ እእላፍ ፡ መላእክቶች ፡ ወድቀው ፡ የሚሰግዱልህ
በእውነት ፡ አንተ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህ (፪x)

አዝ:- በእውነት ፡ እኛም ፡ አናውቅህ ፡ እግዚአብሔር ፡ ትልቅ ፡ ነህ
ከአእምሮአችን ፡ በላይ ፡ ጥልቅ ፡ ነው ፡ ችሎታህ
ሥራዎችን ፡ ሁሉ ፡ ስለ ፡ አንተ ፡ አወሩ
ይሁን ፡ ስትላቸው ፡ ሆኑ ፡ ፍጥረታት ፡ በሙሉ
ክብር ፡ ለሥምህ ፡ ይሁን (፪x)