Daniel Amdemichael/Yesew Ej Yelielebet/Yesew Ej Yelielebet

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ርዕስ የሰው እጅ የሌለበት ዳንኤል አምደሚካኤል አልበምየሰው እጅ የሌለበት

አዝ አዳነኝ በፀጋው አመሰግናለሁ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወቴ ጌታ ነው አምላክ በምህረቱ ባዘጋጀው መንገድ በወንጌሉ እምነት ሰጠኝ ዳግም ልደት

በደስታ ከመዘመር ከማመስገን በቀር እኔማ ምን ልከፍል ከቶ ምን ልናገር የሰው እጅ የሌለበት የእኔ ብሎ የሚያኮራ በማመን የሚገኝ ጽድቅ የመስቀሉን ስራ

ፀጋው በእምነት ሆኖ አድኖኛል እግዚአብሔር በልጁ ሕይወትን ሰጥቶኛል ሁሉ ተፈጸመ በመስቀሉ በሰላም እንድኖር በዘለዓለም ፍቅሩ

ላመስግነው በዝማሬ ይኼን ታላቅ ጌታ ከጨለማ ለነጠቀኝ ከዚያ ክፉ ቦታ ለወደደኝ ብርሃኑን ላበራ በሕይወቴ መልካም ዜማ ለእርሱ ይሁን ይክበር መድሃኒቴ

አምላክ አበጃጀው ዘለዓለሜን አንድ ልጁን ሰጥቶ ክርስቶስ ብቃቴን የዘለላእም ህብረት ከአብ ጋራ አገኘሁ ልጅነት በክርስቶስ ስራ

ምሥጋናውን ልዘምረው ልናገር ወንጌሉን ጌታ ኢየሱስ እንደሚያድን ላብስር ምስራቹን የአምላክ ፍቃድ ኢኼ ሆኗል ሰዎን የሚያመልጡበት በልጁ ደም በእግዚአብሔር ጽድቅ አምነው ሚድኑበት

አዝ አዳነኝ በፀጋው አመሰግናለሁ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወቴ ጌታ ነው አምላክ በምህረቱ ባዘጋጀው መንገድ በወንጌሉ እምነት ሰጠኝ ዳግም ልደት

በደስታ ከመዘመር ከማመስገን በቀር እኔማ ምን ልከፍል ከቶ ምን ልናገር የሰው እጅ የሌለበት የእኔ ብሎ የሚያኮራ በማመን የሚገኝ ጽድቅ የመስቀሉን ስራ

ምሥጋና ለአምላክ ፍቅር ለታደገኝ እግሬን ከጨለማ መንገድ መለሰልኝ ብርሃንን አሳየኝ ቅዱስ ቃሉ ተፈጸመ እንዳለ ጌታ በመስቀሉ


ባመሰግን ይበዛል ወይ እኔስ በየእለቱ ቅኔ ብቀኝ ባሸበሸብ ብዘምር በቤቱ እልልስ ብል በታላቅ ድምጽ ብጮህ እስከደስታ ባጨበጭብ በመቅደሱ ለዚህ ክቡር ጌታ

አዝ አዳነኝ በፀጋው አመሰግናለሁ ኢየሱስ ክስቶስ የሕይወቴ ጌታ ነው አምላክ በምህረቱ ባዘጋጀው መንገድ በወንጌሉ እምነት ሰጠኝ ዳግም ልደት

በደስታ ከመዘመር ከማመስገን በቀር እኔማ ምን ልከፍል ከቶ ምን ልናገር የሰው እጅ የሌለበት የእኔ ብሎ የሚያኮራ በማመን የሚገኝ ጽድቅ የመስቀሉን ስራ አሃ (፬x)