በሰማይ ፡ ዙፋኑ (Besemay Zufanu) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 6.jpg


(6)

የሰው ፡ እጅ ፡ የሌለበት
(Yesew Ej Yelielebet)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(7)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

 
አዝ፦ በሠማይ ፡ ዙፋኑ ፡ በመቅደሱ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ፈጣሪ ፡ እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው
ዓይኑ ፡ እንዳየ ፡ አይፈርድ ፡ ጆሮው ፡ እንደሰማ
በምክሩ ፡ ትክክል ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ እርሱማ
ልብን ፡ ለይቶ ፡ የሚመረምረው
እንደሰው ፡ አይደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጻዲቅ ፡ ነው

የሚያድን ፡ ነው ፡ ደግሞ ፡ የሚራራ
አቤቱ ፡ ማረኝ ፡ ላለ
ወደ ፡ እርሱ ፡ ለተጠጋ
ውድ ፡ ልጁ ፡ በመረቀልን ፡ በር
ወደ ፡ እርሱ ፡ መግባት ፡ አለ ፡ አሄ
ታላቅ ፡ ስሙ ፡ ይክበር

በምክሩ ፡ ጠቢብ ፡ ፍቅሩ ፡ የላቀ
በልጆቹ ፡ ላይ ፡ ግርማው ፡ የደመቀ
ምሥጋና ፡ ሞላ ፡ በማደሪያው ፡ ላይ
በመንጋው ፡ መልካም ፡ ማዳኑን ፡ ሲታይ

አዝ፦ በሠማይ ፡ ዙፋኑ ፡ በመቅደሱ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ፈጣሪ ፡ እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው
ዓይኑ ፡ እንዳየ ፡ አይፈርድ ፡ ጆሮው ፡ እንደሰማ
በምክሩ ፡ ትክክል ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ እርሱማ
ልብን ፡ ለይቶ ፡ የሚመረምረው
እንደሰው ፡ አይደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጻዲቅ ፡ ነው

ታናሹን ፡ ሰው ፡ ለክብር ፡ የሚያበቃው
የዳዊት ፡ የሙሴ ፡ አምላክ ፡ አሄ ፡ ለትሁቱ ፡ ጠበቃ
የወህኒውን ፡ መዝጊያ ፡ የሚሰብር
ለባሪያዎቹ ፡ ፈራጅ ፡ የሚሆን ፡ ሞገስ ፡ ክብር

አቢት ፡ እግዚአብሔር ፡ ስራው ፡ ድንቅ ፡ ነው
በመልካም ፡ ዜማ ፡ እስቲ ፡ እናምልከው
ክብሩ ፡ ይታወጅ ፡ በቤቱ ፡ መድረክ
የዘለዓለሙ ፡ አምላክ ፡ ይባረክ

አዝ፦ በሠማይ ፡ ዙፋኑ ፡ በመቅደሱ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ፈጣሪ ፡ እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው
ዓይኑ ፡ እንዳየ ፡ አይፈርድ ፡ ጆሮው ፡ እንደሰማ
በምክሩ ፡ ትክክል ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ እርሱማ
ልብን ፡ ለይቶ ፡ የሚመረምረው
እንደሰው ፡ አይደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጻዲቅ ፡ ነው

ተራሮችን ፡ ከላይ ፡ የሚያጠጣ
ለጻድቅ ፡ ለሃጥኡ ፡ አሄ ፡ ፀሐይን ፡ የሚያወጣ
ደረቁን ፡ ምድር ፡ የሚያለመልመው
ለታናሹ ፡ ሰው ፡ ብርታት ፡ እህ ፡ ሞገስ ፡ የሚሰጠው

ምሥጋናን ፡ ያምጡ ፡ ለእርሱ ፡ ያደሩ
በመንፈሱ ፡ ኃይል ፡ እየዘመሩ
የቤቱ ፡ ካህናት ፡ ምስክሮቹ
ስሙን ፡ ያክብሩ ፡ ታማኝ ፡ ባሮቹ

አዝ፦ በሠማይ ፡ ዙፋኑ ፡ በመቅደሱ ፡ ያለው
የፍጥረት ፡ ፈጣሪ ፡ እግዚአብሔር ፡ ድንቅ ፡ ነው
ዓይኑ ፡ እንዳየ ፡ አይፈርድ ፡ ጆሮው ፡ እንደሰማ
በምክሩ ፡ ትክክል ፡ ታማኝ ፡ ነው ፡ እርሱማ
ልብን ፡ ለይቶ ፡ የሚመረምረው
እንደሰው ፡ አይደለ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጻዲቅ ፡ ነው