ይጠብቀኛል (Yetebeqegnal) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(10)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

አዝ:- በቀንም ፡ በሌሊት ፡ ጌታዬ ፡ ይጠብቀኛል
አሃአሃ ፡ ይጠብቀኛል ፡ እህእህ
እንደ ፡ አምላኬ ፡ ያለ ፡ ከወዴት ፡ ይገኛል
አሃአሃ ፡ ከየት ፡ ይገኛል ፡ ሆሆሆ ፡ ከየት ፡ ይገኛል

መውጣቴ ፡ መግባቴ ፡ ከእርሱ ፡ ተጠብቆ
ባለፍኩበት ፡ መንገድ ፡ ጌታ ፡ ለእኔ ፡ ተተንቅቆ
በምህረቱ ፡ ታድጓታል ፡ ነፍሴን ፡ ከእሳት ፡ ነጥቆ
የእርሱን ፡ ደግነት ፡ ለሰው ፡ እነግራለው
አያሳፍርም ፡ ሁሌ ፡ ታማኝ ፡ ነው
በሥም ፡ የሚያውቀኝ ፡ የሆነኝ ፡ ጥላ
ኢየሱስ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ ከለላ

አዝ:- በቀንም ፡ በሌሊት ፡ ጌታዬ ፡ ይጠብቀኛል
አሃአሃ ፡ ይጠብቀኛል ፡ እህእህ
እንደ ፡ አምላኬ ፡ ያለ ፡ ከወዴት ፡ ይገኛል
አሃአሃ ፡ ከየት ፡ ይገኛል ፡ ሆሆሆ ፡ ከየት ፡ ይገኛል

ትንፋሼን ፡ መንገዴን ፡ በእጁ ፡ ለያዘው
የሰማዩን ፡ ፍቅር ፡ ሰላም ፡ ውስጤ ፡ ላፈሰሰው
በማዳኑ ፡ ደስ ፡ እያለኝ ፡ አመሰግናለሁ
ታሪክም ፡ የለኝ ፡ ታሪኬ ፡ እርሱ ፡ ነው
ከልጅነቴ ፡ እጄን ፡ የያዘው
ምስክሩ ፡ ነኝ ፡ ዘለዓለም ፡ ይንገሥ
መልካም ፡ እረኛ ፡ ስሙ ፡ ኢየሱስ

አዝ:- በቀንም ፡ በሌሊት ፡ ጌታዬ ፡ ይጠብቀኛል
አሃአሃ ፡ ይጠብቀኛል ፡ እህእህ
እንደ ፡ አምላኬ ፡ ያለ ፡ ከወዴት ፡ ይገኛል
አሃአሃ ፡ ከየት ፡ ይገኛል ፡ ሆሆሆ ፡ ከየት ፡ ይገኛል