ምህረቱን ፡ አይቼ ፡ ነው (Meheretun Ayechie New) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(6)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

የጌታን ፡ ቸርነት ፡ ምህረቱን ፡ ሳስበው
መውጣቴ ፡ መግባቴ ፡ መኖሬ ፡ በእርሱ ፡ ነው
ለእኔ ፡ የበዛው ፡ ፍቅር ፡ እጅግ ፡ ይገርመኛል
ሁሌ ፡ ሳታቋርጥ ፡ አመስግን ፡ ይለኛል

እጆቼን ፡ ወደ ፡ ጌታ ፡ ወደ ፡ ኢየሱስ ፡ ዘርግቼ
አመሰግነዋለሁ ፡ ስለተዋቡት ፡ ቀኖቼ
ኢየሱስ ፡ ሕያው ፡ አለት ፡ የኔ ፡ ጽኑ ፡ መሰረት
ምሥጋና ፡ ይብዛህ ፡ እንጂ ፡ ምሥጋና ፡ አይነስበት

አዝ:- ምህረቱን ፡ አይቼ ፡ ነው ፡ ፍቅሩን ፡ ቀምሼ ፡ ነው
ዛሬ ፡ ደስ ፡ ብሎኝ ፡ በፊቱ ፡ ቆሜ ፡ ምዘምረው (፪x)

በአባትነት ፡ ፍቅሩ ፡ ሁሌ ፡ እየመከረኝ
እግሬ ፡ ሲንሸራተት ፡ ይዞ ፡ እየደገፈኝ
በጸጋው ፡ ከልሎ ፡ እዚህ ፡ አድርሶኛል
እንዳመሰግነው ፡ ውስጤ ፡ ግድ ፡ ይለኛል

ልዘምር ፡ ለጌታዬ ፡ እርሱ ፡ ምሥጋናዬ ፡ ነው
እግሬን ፡ እመሰናከል ፡ ነፍሴ ፡ ከሞት ፡ ላዳነው
ልቅረብ ፡ በፊቱ ፡ ልስገድ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ወዶኛል
ሁልጊዜ ፡ ጠዋት ፡ አማታ ፡ ሳመልከው ፡ ደስ ፡ ይለኛል

አዝ:- ምህረቱን ፡ አይቼ ፡ ነው ፡ ፍቅሩን ፡ ቀምሼ ፡ ነው
ዛሬ ፡ ደስ ፡ ብሎኝ ፡ በፊቱ ፡ ቆሜ ፡ ምዘምረው (፪x)

ተአምራቱን ፡ ያየ ፡ ፍቅር ፡ የበዛለት
ድንቁ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ሞገስ ፡ የሆነለት
ሳይቆጥብ ፡ ይናገር ፡ ያውራ ፡ የእርሱን ፡ ስራ
ተአምር ፡ እንደሚያድርግ ፡ ድንቅን ፡ እንደሚሰራ

ይናገር ፡ የቀመሰ ፡ ፍቅሩን ፡ መልካምነቱን
የሚያድን ፡ የሚታደግ ፡ ብሩህ ፡ አባት ፡ መሆኑን
አምላክ ፡ ነው ፡ የሚያስመካ ፡ እረዳት ፡ ድንቅ ፡ ሰሪ
ዘመኑ ፡ ቁጥር ፡ የለው ፡ ጌታ ፡ ዘለዓለም ፡ ነዋሪ

አዝ:- ምህረቱን ፡ አይቼ ፡ ነው ፡ ፍቅሩን ፡ ቀምሼ ፡ ነው
ዛሬ ፡ ደስ ፡ ብሎኝ ፡ በፊቱ ፡ ቆሜ ፡ ምዘምረው (፪x)