ኢየሱስ (Eyesus) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 5.png


(5)

ሰላም
(Selam)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

ያ ፡ የጥንቱ ፡ ፍቅራችን ፡ መሃላችን ፡ የታለ
ኀጢአታችን ፡ በዝቶ ፡ ጥላቻን ፡ አበቀለ
ከአንተ ፡ ያልተቀበልነው ፡ ያልሰጠኸን ፡ ምን ፡ አለ
ሁሉም ፡ ተረስቶ ፡ ዛሬ ፡ ትዕቢታችን ፡ ከፍ ፡ አለ

አዝ:- ኢየሱስ (፪x) ፡ በማስተዋል ፡ ሙላን ፡ በማስተዋል (፪x)

ኀጢአት ፡ ከንቱ ፡ ነው ፡ አይሆንም ፡ ልማት
ሞትን ፡ ይወልዳል ፡ ለሕይወት ፡ ጥፋት
ደሙ ፡ ያላጠበው ፡ ያልተመለሰ
እናስብ ፡ እንጂ ፡ ከየት ፡ ደረሰ
ምክንያት ፡ አንደርድር ፡ ለድካማችን
ከሞት ፡ ያድናል ፡ መመለሳችን
ኑሯችን ፡ ከንቱ ፡ ከእውነት ፡ የሚጣረስ
ንሰሃ ፡ እንግባ ፡ ሳናለባብስ

ቦታ ፡ አጥቶ ፡ ቅድስና ፡ ኀጢአት ፡ ተሞልቷል ፡ ቤቱ
ሁሉም ፡ አንተን ፡ አልፈራም ፡ ይስታል ፡ በአንደበቱ
የጥበብ ፡ መጀመሪያው ፡ አንተን ፡ መፍራቱ ፡ ጠፍቶ
ሁሉ ፡ እንዳሻው ፡ ይሄዳል ፡ ቤቱ ፡ በአመጽ ፡ ተሞልቶ

አዝ:- ኢየሱስ (፪x) ፡ በማስተዋል ፡ ሙላን ፡ በማስተዋል (፪x)

ከየት ፡ ተማርነው ፡ ወንድምን ፡ መጥላት
ከነብያት ፡ ነው ፡ ወይንስ ፡ ከሓዋርያት
የቀደሙትን ፡ የምናውቃቸው ፡ በመልካም ፡ ፍቅር ፡ በጸሎታቸው
ለእውነት ፡ እንኑር ፡ ከቶ ፡ አንገበዝ
ደሙ ፡ ያነጻናል ፡ ቶሎ ፡ እንመለስ
የሰማይ ፡ ጥበብ ፡ የላይኛይቱን
ከአምላክ ፡ እንለምን ፡ ይሰማል ፡ ሁሉን (፪x)