የሕይወቴ ፡ ሚስጥር (Yehiwotie Mister) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 1.jpg


(1)

አንበሳ
(Anbesa)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፹ ፰ (1996)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 6:26
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

የሕይወት ፡ ሚስጥር ፡ ሳይገባቸው ፡ ሲከተሉ ፡ ለእንጀራቸው
አልተስማሙም ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ ተመለሱ ፡ ወደ ፡ ኋላ
እኔስ ፡ በርቶልኛል ፡ መዳን ፡ ሆኖልኛል
ሕይወት ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ ኢየሱስ ፡ የለህ ፡ አቻ

አዝ፦ ምንም ፡ ላላገኝ ፡ ከአንተ ፡ ርቄ ፡ ላይሆንልኝ
ጥሜ ፡ ላይረካ ፡ የዓለም ፡ ኑሮ ፡ ላይፈይደኝ
ከአንተ ፡ ወዴት ፡ እሄዳለሁኝ ፡ ኢየሱስ ፡ እንደ ፡ አንተ
ለእኔ ፡ የሚሆን ፡ መቼም ፡ ቢሆን ፡ አላየሁኝ (፪x)

መድኃኒቴ ፡ አንተ ፡ ልዩ ፡ ነህ ፡ ማንም ፡ የለም ፡ የሚመስልህ
ኢየሱስ ፡ ለእኔ ፡ መከታዬ ፡ ጋሻዬ ፡ ነህ ፡ ከለላዬ
ከአንተ ፡ አልለይም ፡ ሌላው ፡ አይሆንልኝም
የሕይወት ፡ ቃል ፡ አለህ ፡ ጥሜን ፡ ታረካለህ

አዝ፦ ምንም ፡ ላላገኝ ፡ ከአንተ ፡ ርቄ ፡ ላይሆንልኝ
ጥሜ ፡ ላይረካ ፡ የዓለም ፡ ኑሮ ፡ ላይፈይደኝ
ከአንተ ፡ ወዴት ፡ እሄዳለሁኝ ፡ ኢየሱስ ፡ እንደ ፡ አንተ
ለእኔ ፡ የሚሆን ፡ መቼም ፡ ቢሆን ፡ አላየሁኝ (፪x)

ከአንተ ፡ ጋር ፡ ኑሮ ፡ ተመችቶኛል ፡ ኢየሱሴ ፡ ጉያህ : ሞቆኛል
በፍቅርህ ፡ ነው ፡ እኔን ፡ የሳብከኝ ፡ እስከሞት ፡ ድረስ ፡ የወደድከኝ
በቃ ፡ ወስኛለሁ ፡ አንተን ፡ መርጫለሁ
እርስቴ ፡ ነህ ፡ ብያለሁ ፡ ከአንተ ፡ ወዴት ፡ እሄዳለሁ

አዝ፦ ምንም ፡ ላላገኝ ፡ ከአንተ ፡ ርቄ ፡ ላይሆንልኝ
ጥሜ ፡ ላይረካ ፡ የዓለም ፡ ኑሮ ፡ ላይፈይደኝ
ከአንተ ፡ ወዴት ፡ እሄዳለሁኝ ፡ ኢየሱስ ፡ እንደ ፡ አንተ
ለእኔ ፡ የሚሆን ፡ መቼም ፡ ቢሆን ፡ አላየሁኝ (፪x)

ኢየሱስ ፡ ሕይወቴን ፡ አብርተሃል ፡ እኔነቴን ፡ ለውጠሃል
አልለይህም ፡ ወድሃለሁ ፡ ከአንተ ፡ ውጪ ፡ ጨለማ ፡ ነው
ግዛኝ ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ልስገድ ፡ ጠዋት ፡ ማታ
ነፍሴን ፡ የተቤዠህ ፡ አንተው ፡ ትሻሃለኛለህ

አዝ፦ ምንም ፡ ላላገኝ ፡ ከአንተ ፡ ርቄ ፡ ላይሆንልኝ
ጥሜ ፡ ላይረካ ፡ የዓለም ፡ ኑሮ ፡ ላይፈይደኝ
ከአንተ ፡ ወዴት ፡ እሄዳለሁኝ ፡ ኢየሱስ ፡ እንደ ፡ አንተ
ለእኔ ፡ የሚሆን ፡ መቼም ፡ ቢሆን ፡ አላየሁኝ (፪x)