መስማማት (Mesmamat) - ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳንኤል ፡ አምደሚካኤል
(Daniel Amdemichael)

Daniel Amdemichael 1.jpg


(1)

አንበሳ
(Anbesa)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፹ ፰ (1996)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 6:06
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳንኤል ፡ አምደሚካኤል ፡ አልበሞች
(Albums by Daniel Amdemichael)

ሀሳቤ ፡ የልቤ ፡ ባይሞላ
ያቀድኩት ፡ ነገር ፡ ባይሰካ
ላመስግን ፡ ልተው ፡ ማማረሬን
ያልከው ፡ ይሁን ፡ ጌታ
ያ ፡ መልካም ፡ ነው ፡ ለእኔ

አዝ፦ ከአንተ ፡ ጋር ፡ መስማማት ፡ ይሻላል
መማረር ፡ ማኩረፍ ፡ ምን ፡ ያዋጣል
ፈቃድህ ፡ ይሁን ፡ ማለት ፡ መልካም
በጊዜው ፡ ነገር ፡ ውብ ፡ ይሆናል (፪x)

ችግሬ ፡ ረሃቤ ፡ ቢፀናም
ቁስሌ ፡ ባይደርቅ ፡ ፈውሴ ፡ ቢዘገይ
ከፈቀድከው ፡ ይሁን ፡ ማለት
አስተምረኝ ፡ ጌታዬ ፡ ትግስትን

አዝ፦ ከአንተ ፡ ጋር ፡ መስማማት ፡ ይሻላል
መማረር ፡ ማኩረፍ ፡ ምን ፡ ያዋጣል
ፈቃድህ ፡ ይሁን ፡ ማለት ፡ መልካም
በጊዜው ፡ ነገር ፡ ውብ ፡ ይሆናል (፪x)

ጌታ ፡ ነህ ፡ ብትገል ፡ ብታድንም
መከራከር ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ኣይበጅም
ክፉ ፡ አይደለህም ፡ ጨካኝ
ለአላማህ : ነው ፡ ጌታ: የምትመራኝ

አዝ፦ ከአንተ ፡ ጋር ፡ መስማማት ፡ ይሻላል
መማረር ፡ ማኩረፍ ፡ ምን ፡ ያዋጣል
ፈቃድህ ፡ ይሁን ፡ ማለት ፡ መልካም
በጊዜው ፡ ነገር ፡ ውብ ፡ ይሆናል (፪x)

አንተ ፡ ያልከው ፡ ይሻለኛል
የእራሴማ ፡ መቼ ፡ ያዋጣኛል
ትርፉ ፡ መመረር ፡ መቁሰል ፡ ነው
ለአንተ ፡ ሀሳብ :ጌታ ፡ መገዛት ፡ ጥሩ ፡ ነው

አዝ፦ ከአንተ ፡ ጋር ፡ መስማማት ፡ ይሻላል
መማረር ፡ ማኩረፍ ፡ ምን ፡ ያዋጣል
ፈቃድህ ፡ ይሁን ፡ ማለት ፡ መልካም
በጊዜው ፡ ነገር ፡ ውብ ፡ ይሆናል (፪x)

በሥራህ ፡ ሁልጊዜ ፡ ጻድቅ ፡ ነህ
ተሳስተህስ ፡ መቼ ፡ ታውቃለህ
ሀሳቤን ፡ በሀሳብህ ፡ ጠቅልለው
ምኞቴንም ፡ ኢየሱስ ፡ እንደ ፡ ቃልህ ፡ አርገው

አዝ፦ ከአንተ ፡ ጋር ፡ መስማማት ፡ ይሻላል
መማረር ፡ ማኩረፍ ፡ ምን ፡ ያዋጣል
ፈቃድህ ፡ ይሁን ፡ ማለት ፡ መልካም
በጊዜው ፡ ነገር ፡ ውብ ፡ ይሆናል (፪x)