ይሰራል ፡ ጌታ (Yeseral Gieta) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 4.jpg


(4)

ቃልህ ፡ ቃሌና ፡ ግብሬ
(Qaleh Qaliena Gebrie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2010)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

አምላኬማ ፡ አምላክ ፡ ነውና ፡ ዛሬም ፡ ይኖራል
ሳይለወጥ ፡ እየለወጠ ፡ ታሪክ ፡ ይሰራል
አምላኬማ ፡ አምላክ ፡ ነውና ፡ ዛሬም ፡ ይኖራል
ሳይቀየር ፡ እየቀየረ ፡ ታሪክ ፡ ይሰራል

ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ እጅ
አይቻለሁኝ ፡ ሁሉን ፡ ሲያበጅ
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ ቃል
ያለ ፡ ምሰሶ ፡ ሰማይ ፡ ቆሟል
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ እጅ
አይቻለሁኝ ፡ ሁሉን ፡ ሲያበጅ
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ ቃል
ስንት ፡ ደካማ ፡ በዚያ ፡ ቆሟል

አዝ፦ አቤት ፡ አቤት ፡ ሥራህ
እኔስ ፡ ጌታ ፡ ወደድኩልህ/አየሁልህ (፪x)

ስለ ፡ ጌታ ፡ የሚባል ፡ ብዙ ፡ ነገር ፡ ኖሮ
እንዴት ፡ ልቤ ፡ ይግባ ፡ ሀዘን ፡ እንጉርጉሮ
እንደሰው ፡ ልጅ ፡ ሀሳብ ፡ አይደለም ፡ መንገዱ
ለበጎ ፡ ነው ፡ እንጀ ፡ እሱን ፡ ለወደዱ

አዝ፦ አቤት ፡ አቤት ፡ ሥራህ
እኔስ ፡ ጌታ ፡ ወደድኩልህ/አየሁልህ (፪x)

ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ እጅ
አይቻለሁኝ ፡ ሁሉን ፡ ሲያበጅ
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ ቃል
ያለ ፡ ምሰሶ ፡ ሰማይ ፡ ቆሟል
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ እጅ
አይቻለሁኝ ፡ ሁሉን ፡ ሲያበጅ
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ ቃል
ስንት ፡ ደካማ ፡ በዚያ ፡ ቆሟል

በመጀመሪያ ፡ በፍጥረት ፡ ዓለም
ግዑዝም ፡ ሕያው ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ የለም
ሁሉን ፡ ካመጣህ ፡ ከምንም ፡ ነገር
ዛሬም ፡ ስለ ፡ እኔ ፡ ተናግረህ ፡ አይቀር

አዝ፦ አቤት ፡ አቤት ፡ ሥራህ
እኔስ ፡ ጌታ ፡ ወደድኩልህ/አየሁልህ (፪x)

ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ ሥም
ወደ ፡ ላይ ፡ አይሄድም ፡ ደፍሮ ፡ ማንም
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ መንፈስ
ወደ ፡ እውነት ፡ ሁሉ ፡ መርቶ ፡ ሚመልስ
ይሰራል ፡ ጌታ ፡ የአንተ ፡ ሕግ
ፍትህ ፡ ያለበት ፡ ፍርድ ፡ የሚያደርግ

አዝ፦ አቤት ፡ አቤት ፡ ሥራህ
እኔስ ፡ ጌታ ፡ ወደድኩልህ/አየሁልህ (፪x)

የተዋበና ፡ የተራቀቀ
የአምላኬ ፡ ሥራ ፡ እጅግ ፡ የላቀ
መፈጠር ፡ እንጂ ፡ መፍጠር ፡ ማን ፡ ችሏል
ማደስ ፡ ብቻ ፡ አይደል ፡ አዲስ ፡ ይሰራል

አዝ፦ አቤት ፡ አቤት ፡ ሥራህ
እኔስ ፡ ጌታ ፡ ወደድኩልህ/አየሁልህ (፪x)