ትክክል ፡ እውነተኛ (Tekekel Ewnetegna) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 2.jpg


(2)

ጌታ ፡ አለ ፡ ከጐኔ
(Gieta Ale Kegonie)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 4:24
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

አምኜው ፡ አልከዳኝም
በእኔ ፡ ላይ ፡ አልፈረደም (፪x)

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ የእኔ ፡ ዳኛ
ትክክል ፡ እውነተኛ (፪x)

ሰው ፡ ፊትን ፡ አይቶ ፡ ሲፈርድ ፡ ጌታ ፡ ግን ፡ የልብን ፡ ነው
ሁሉንም ፡ እንደስራው ፡ አይቶ ፡ ነው ፡ የሚከፍለው
በፍርዱ ፡ አይጸጸት ፡ ለካ ፡ እንዲህ ፡ ነበር ፡ አይል
አስተዋይ ፡ ጥበበኛ ፡ እርሱ ፡ ነው ፡ የኔ ፡ ዳኛ

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ የእኔ ፡ ዳኛ
ትክክል ፡ እውነተኛ (፪x)

እግዚአብሔር ፡ ክንደ ፡ ብርቱ ፡ ተቀምጦ ፡ በችሎቱ
አይፈራ ፡ አያዳላ ፡ አይዋሽም ፡ እንደሌላ
አፉ ፡ በፍርድ ፡ አይስት ፡ ሚዛኑ ፡ ትክክል ፡ ነው
በእኔ ፡ ላይ ፡ ሳይሆን ፡ ለእኔ ፡ ፈረደልኝ ፡ መድህኔ

ዳኛዬ ፡ እሱ ፡ ነው ፡ የእኔ ፡ ዳኛ (፬x)

በግራና ፡ በቀኙ ፡ አማካሪ ፡ አይፈልግም
ቃሉንም ፡ የሚያርመው ፡ ከቶ ፡ አንድም ፡ አይገኝም
እግዚአብሔር ፡ አዋቂ ፡ ነው ፡ ሥራውን ፡ ይመዝናል
ውሳኔው ፡ መጨረሻው ፡ የእኔን ፡ ልብ ፡ አሳርፏል

አዝ፦ እግዚአብሔር ፡ የእኔ ፡ ዳኛ
ትክክል ፡ እውነተኛ (፪x)