ሲነድ ፡ ይሰማኛል (Sined Yesemagnal) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 2.jpg


(2)

ጌታ ፡ አለ ፡ ከጐኔ
(Gieta Ale Kegonie)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)

ርዝመት (Len.): 4:14
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

የፍቅርህ ፡ ልክ ፡ የፍቅርህ ፡ ገደብ
በዝቶብኝ ፡ እኔስ ፡ ለማሰብ
አይጠፋም ፡ ሥምህ ፡ ከአፌ
አይወጣም ፡ ፍቅርህ ፡ ከልቤ (፪x)

ቀስቃሽ ፡ አልፈልግም ፡ ሳመልክህ
መች ፡ በረደ ፡ ውስጤ ፡ ያ ፡ ፍቅርህ
ሲነድ ፡ ይሰማኛል ፡ በላዬ
እወድሃለሁኝ ፡ ጌታዬ (፪x)

ኢየሱሴ ፡ ለኔ ፡ ምትክ ፡ የለህ
ልቤም ፡ ሌላ ፡ አይሻ ፡ አንተ ፡ እያለህ
ከፍ ፡ የምታደርግ ፡ በአንተ ፡ ጊዜ
ዙፋንህ ፡ ሥር ፡ ልስገድ ፡ ሁልጊዜ

ተባረካ ፡ ጌታዬ ፡ ተባርክ
ተባረካ ፡ አምላኬ ፡ ተባረክ (፪x)

ምን ፡ ይከፈልሃል ፡ ጌታዬ ፡ (አሃሃ) ፡ ጌታዬ
ሁሉ ፡ የአንተ ፡ ነው ፡ አምላኬ ፡ (አሃሃ) ፡ አምላኬ
ምሥጋናና ፡ አምልኮ ፡ አምልኮ ፡ (አሃሃ) ፡ ምሥጋና
መቼ ፡ ይበዛብሃል ፡ ትልቅ ፡ ነህ ፡ (አሃሃ) ፡ ገናና

ተመስገንልኝ ፡ ጌታዬ ፡ ተመስገንልኝ
ከሕያዋን ፡ ጋር ፡ ሥምህን ፡ አከብራለሁኝ
ተባረክልኝ ፡ ጌታዬ ፡ ተባረክልኝ
ከሚወዱህ ፡ ጋር ፡ ሥምህን ፡ አከብራለሁኝ

እንዳለፈ ፡ ውሃ ፡ መከራዬን
ረስቼዋለሁ ፡ ሳየው ፡ ጌታን
እኔስ ፡ አልሰጋም ፡ ከእንግዲህስ ፡ ብዬ
እዚህ ፡ ያደረስኝ ፡ አለ ፡ ጌታዬ

አለ ፡ ጌታዬ ፡ (አለ) (፰x)