አመሰግናለሁ (Amesegnalehu) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 2.jpg


(2)

ጌታ ፡ አለ ፡ ከጐኔ
(Gieta Ale Kegonie)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 5:06
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

አዝ፦ የልቤ ፡ ደረሰ ፡ ያሰብኩት ፡ ተሳካ
አደራ ፡ የሰጠሁት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ለካ (፪x)

ዛሬማ ፡ አርፌ ፡ ተደላድያለሁ
ሥራዬ ፡ ተሰርቶ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)

በሬን ፡ ዘግቼ ፡ የለመንኩት
ምነው ፡ ባረገው ፡ ጌታን ፡ ያልኩት
በእጥፍ ፡ ላከው ፡ ቀዶ ፡ ከሰማይ
የልቤ ፡ ደርሷል ፡ ካሰብኩት ፡ በላይ (፪x)

አዝ፦ የልቤ ፡ ደረሰ ፡ ያሰብኩት ፡ ተሳካ
አደራ ፡ የሰጠሁት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ለካ (፪x)

ዛሬማ ፡ አርፌ ፡ ተደላድያለሁ
ሥራዬ ፡ ተሰርቶ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)

የጌታን ፡ ውለታ ፡ በጥዋት ፡ በማታ
መች ፡ እዘነጋለሁ ፡ እዘምረዋለሁ
የጌታን ፡ ውለታ ፡ በጥዋት ፡ በማታ
መች ፡ እዘነጋለሁ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)

አዝ፦ የልቤ ፡ ደረሰ ፡ ያሰብኩት ፡ ተሳካ
አደራ ፡ የሰጠሁት ፡ ኢየሱስ ፡ ነው ፡ ለካ (፪x)

ዛሬማ ፡ አርፌ ፡ ተደላድያለሁ
ሥራዬ ፡ ተሰርቶ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)

(የልቤ ፡ ደረሰ) (፫x)

አላየሁኝም ፡ ፃድቅ ፡ ሲጣል
ዘሩም ፡ ሲለምን ፡ አጥቶ ፡ እህል
ጌታ ፡ ታሪኬን ፡ እንዲህ ፡ አርጐታል
የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ አሳክቶታል (፪x)

የጌታን ፡ ውለታ ፡ በጥዋት ፡ በማታ
መች ፡ እዘነጋለሁ ፡ እዘምረዋለሁ
የጌታን ፡ ውለታ ፡ በጥዋት ፡ በማታ
መች ፡ እዘነጋለሁ ፡ አመሰግናለሁ (፪x)