ላመስግነው (Lamesgenew) - ዳግማዊ ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ዳግማዊ ፡ ጥላሁን
(Dagmawi Tilahun)

Dagmawi Tilahun 3.jpg


(3)

ፍቅር ፡ ይቅር ፡ ያለው
(Feqer Yeqer Yalew)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2009)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የዳግማዊ ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Dagmawi Tilahun)

ዙሪያዬን ፡ ሳይ ፡ ለመዳኔ ፡ ሰው ፡ የለኝም ፡ አንድ ፡ ለእኔ
ሰድበኸው ፡ ሙት ፡ አትበሉኝ ፡ ለእኔው ፡ ጥቅም ፡ ሲፈትነኝ
ሁሉ ፡ እያለ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ አፌ ፡ ከንቱ ፡ መቼ ፡ አወራ
ለማመስገን ፡ ለውዳሴ ፡ ይበቃኛል ፡ እስትንፋሴ

አዝ፦ ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ እንባዬ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ሀዘኔ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ለቅሶዬ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ሀዘኔ ፡ ላመስግነው

የሰጠውን ፡ ጌታ ፡ ቢነሳ ፡ ስላለው ፡ ነው ፡ ያን ፡ የሚያስረሳ
ሊያልፍ ፡ ነገር ፡ አላማርርም ፡ ምሥጋናዬን ፡ አላጓድልም
የሰጠውን ፡ ጌታ ፡ ቢወስደው ፡ ስላለው ፡ ነው ፡ ያን ፡ የሚበልጠው
ሊያልፍ ፡ ነገር ፡ አላማርርም ፡ ምሥጋናዬን ፡ አላጓድልም

ላመስግነው ፡ ቢጐድልም ፡ ቢሞላ ፡ ላመስግነው ፡ አምላክ ፡ የለኝ ፡ ሌላ
ላመስግነው ፡ ዛሬ ፡ ያለኝ ፡ ቢነሳ ፡ ላመስግነው ፡ ትላንትን ፡ አልረሳ
ላመስግነው ፡ ቢጐድልም ፡ ቢሞላ ፡ ላመስግነው ፡ አምላክ ፡ የለኝ ፡ ሌላ
ላመስግነው ፡ እምነቴ ፡ ቢለካ ፡ ላመስግነው ፡ ለበጐ ፡ ነው ፡ ለካ

ከባርነት ፡ ሲያሻግረኝ ፡ ጠላቶቼን ፡ ሲጥልልኝ
ከበሮ ፡ ይዤ ፡ እንደዘመርኩ ፡ ተዓምራቱን ፡ እንደተረኩ
ዛሬም ፡ ሳልፍ ፡ በበረሃው ፡ አንደኛ ፡ ነኝ ፡ ለምሥጋናው
እየታየኝ ፡ ከፊት ፡ ተስፋ ፡ ላመስግነው ፡ ከምከፋ

አዝ፦ ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ እንባዬ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ሀዘኔ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ለቅሶዬ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ሀዘኔ ፡ ላመስግነው

ላመስግነው ፡ ቢጐድልም ፡ ቢሞላ ፡ ላመስግነው ፡ አምላክ ፡ የለኝ ፡ ሌላ
ላመስግነው ፡ ዛሬ ፡ ያለኝ ፡ ቢነሳ ፡ ላመስግነው ፡ ትላንትን ፡ አልረሳ
ላመስግነው ፡ ቢጐድልም ፡ ቢሞላ ፡ ላመስግነው ፡ አምላክ ፡ የለኝ ፡ ሌላ
ላመስግነው ፡ እምነቴ ፡ ቢለካ ፡ ላመስግነው ፡ ለበጐ ፡ ነው ፡ ለካ

ዙሪያዬን ፡ ሳይ ፡ ለመዳኔ ፡ ሰው ፡ የለኝም ፡ አንድ ፡ ለእኔ
ሰድበኸው ፡ ሙት ፡ አትበሉኝ ፡ ለእኔው ፡ ጥቅም ፡ ሲፈትነኝ
ሁሉ ፡ እያለ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ አፌ ፡ ከንቱ ፡ መቼ ፡ አወራ
ለማመስገን ፡ ለውዳሴ ፡ ይበቃኛል ፡ እስትንፋሴ

አዝ፦ ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ እንባዬ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ሀዘኔ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ለቅሶዬ ፡ ላመስግነው
ላመስግነው ፡ ሲጠበቅ ፡ ሀዘኔ ፡ ላመስግነው