በተቀደሰው (Beteqedesew) - አዜብ ፡ ኃይሉ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዜብ ፡ ኃይሉ
(Azeb Hailu)

Yeqaleh Fechi Yaberal.jpg

የቃልህ ፡ ፍቺ ፡ ያበራል
(Yeqaleh Fechi Yaberal)
ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2013)
ቁጥር (Track):

(8)

ርዝመት (Len.): 6:03
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
ሌሎች ፡ የቡድን ፡ አልበሞች
(Other Collection Albums

አዝ፦ በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻ ፡ እኮ ፡ ነህ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻህን ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ

የቱ ፡ ገብቶኝ ፡ የቱንስ ፡ አውቄ
እንዳስተዋይ ፡ ራሴን ፡ መነቅነቄ
የአንተን ፡ ክብር ፡ የአንተን ፡ ማንነት
ማን ፡ ተረድቶት ፡ ማን ፡ አስተውሎት
ብሞክርም ፡ በቃልህ ፡ ገልጸህ
ከቶ ፡ አልችልም ፡ እንዲህ ፡ ልልህ
ያለኝ ፡ ቋንቋ ፡ በቃ ፡ ይህ ፡ ነውና
እግዚአብሔር ፡ ልበልህ ፡ ገናና

አዝ፦ በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻ ፡ እኮ ፡ ነህ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻህን ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ

በማይታይ ፡ ብርሃን ፡ የደመቀው
መኖሪያህ ፡ በላይ ፡ በሰማያት ፡ ነው
ለዘለዓለም ፡ በቅዱሱ ፡ ስፍራ
የምትኖር ፡ ደግሞ ፡ እየተፈራህ
በስልጣንህ ፡ ሁሉን ፡ የምትገዛ
ባለግርማ ፡ ሞገስህ ፡ የበዛ
ሁሉህ ፡ ከእግርህ ፡ በታች ፡ ተገዝቶልህ
ያለመናወጥ ፡ አንተ ፡ ትኖራለህ

አዝ፦ በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻ ፡ እኮ ፡ ነህ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻህን ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ

ሁሉም ፡ ነገር ፡ ጊዜ ፡ አለው ፡ ሰዓት
ለመውደቁ ፡ ወይ ፡ ለመነሳት
ከፀሐዯ ፡ በታች ፡ አለው ፡ ሁሉ
በየተራ ፡ ይፈራረቃሉ
ተቀያሪ ፡ ተለዋጭ ፡ የሌለህ
ትናንትናም ፡ ዛሬም ፡ ያው ፡ አንተ ፡ ነህ
አይደፈር ፡ ዙፋን ፡ ወንበርህ
እግዚአብሔር ፡ የዘለዓለም ፡ ነህ

አዝ፦ በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻ ፡ እኮ ፡ ነህ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
በተቀደሰው ፡ መቅደስህ
ከፍ ፡ ባለው ፡ ዙፋንህ ፡ ላይ
ያለመናወጥ ፡ ጸንተህ ፡ የምትኖር
አንተ ፡ ብቻህን ፡ ነህ ፡ ጌታዬ ፡ ሆይ




blog comments powered by Disqus