አቤቱ ፡ አምላኬ (Abietu Amlakie) - ቤተልሔም ፡ ወልዴ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቤተልሔም ፡ ወልዴ
(Bethlehem Wolde)

Yeqaleh Fechi Yaberal.jpg

የቃልህ ፡ ፍቺ ፡ ያበራል
(Yeqaleh Fechi Yaberal)
ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2013)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 6:25
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
ሌሎች ፡ የቡድን ፡ አልበሞች
(Other Collection Albums

አዝ፦ አቤቱ ፡ አምላኬ ፡ ከፍ ፡ አደርግሃለሁ
ደግሜ ፡ ደግሜ ፡ ክብርን ፡ እሰጥሃለሁ (፪x)

የማይገባኝን ፡ እኔን ፡ ያስወደደህ
በመስቀል ፡ ላይ ፡ ሞተህ ፡ ነፍስህን ፡ ለእኔ ፡ ሰጠህ
መቼ ፡ ይረሳኛል ፡ ሁሌ ፡ አስበዋለሁ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ አመሰግናለሁ

አዝ፦ አቤቱ ፡ አምላኬ ፡ ከፍ ፡ አደርግሃለሁ
ደግሜ ፡ ደግሜ ፡ ክብርን ፡ እሰጥሃለሁ (፪x)

በማይለወጥ ፡ ፍቅር ፡ እኔን ፡ ወደኸኛል
ለክብርህ ፡ እንዳጥን ፡ አንተ ፡ መርጠኸኛል
ሳልሰለች ፡ ጠዋት ፡ ማታ ፡ አንተን ፡ አመልካለሁ
ለዘለዓለሙ ፡ ክብርን ፡ እሰጥሃለሁ

አዝ፦ አቤቱ ፡ አምላኬ ፡ ከፍ ፡ አደርግሃለሁ
ደግሜ ፡ ደግሜ ፡ ክብርን ፡ እሰጥሃለሁ (፪x)

በእኔ ፡ ዘንድ ፡ ያለ ፡ በአንተ ፡ ዝንድ ፡ የሌለ
ያለ ፡ ነገር ፡ ቢኖር ፡ እሰጥህ ፡ ነበረ
አንተ ፡ ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ ሁሉ ፡ በሁሉ ፡ ነህ
ለውለታህ ፡ ምላሽ ፡ ምሥጋና ፡ ለሥምህ

አዝ፦ አቤቱ ፡ አምላኬ ፡ ከፍ ፡ አደርግሃለሁ
ደግሜ ፡ ደግሜ ፡ ክብርን ፡ እሰጥሃለሁ (፪x)

አስብህና ፡ እደሰታለሁ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ እወድሃለሁ
አስብህና ፡ እደሰታለሁ ፡ የደስታዬ ፡ ምንጭ ፡ እወድሃለሁ
አስብህና ፡ እፎይ ፡ እላለሁ ፡ የእረፍቴ ፡ እወድሃለሁ
አስብህና ፡ እኔ ፡ እርፋለሁ ፡ የእረፍቴ ፡ እወድሃለሁ
አስብህና ፡ እደሰታለሁ ፡ የደስታዬ ፡ ምንጭ ፡ ወድሃለሁ
አስብህና ፡ እደሰታለሁ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱሴ ፡ እወድሃለሁ




blog comments powered by Disqus