ያለ ፡ ደስታ ፡ ስኖር (Yale Desta Senor)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ያለ ፡ ደስታ ፡ ስኖር ፡ ሳለሁ
ክቡር ፡ ደምህ ፡ ፈሰሰልኝ
ምሕረትህን ፡ ላገኝ ፡ መጣሁ
የአምላክ ፡ በግ ፡ መጣሁ ፡ እርዳኝ

ከጨለማ ፡ ልዳን ፡ ብዬ
ሳልዘጋጅ ፡ ለጌታዬ
ጊዜያቱ ፡ አለፈብኝ
የአምላክ ፡ በግ ፡ ና ፡ ውሰደኝ

በምድር ፡ ተንገላትቼ
በችግርና ፡ በጭንቀት
እንደዚህ ፡ ኖርሁ ፡ ተዋግቼ
ና ፡ ና ፡ አድነኝ ፡ ከጭንቀት

መጣሁ ፡ ትቀበለኛለህ
ይቅርታን ፡ ትሰጠኛለህ
የአንተን ፡ ተስፋ ፡ አምነዋለሁ
የአምላክ ፡ በግ ፡ መጣሁ ፡ መጣሁ

አሁን ፡ የአንተ ፡ ፍቅር ፡ አለኝ
ጠላቴን ፡ አስወግድልኝ
የአንተ ፡ ነኝ ፡ የአንተ ፡ ብቻ
አሁን ፡ መጣሁ ፡ ተቀበለኝ