ተመስገን ፡ ጌታዬ ፡ ጥላ ፡ ከለላዬ (Temesgen Gietayie Tela Kelelayie)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን ፡ ጌታዬ ፡ ጥላ ፡ ከለላዬ
በምድር ፡ ላይ ፡ ማን ፡ አለኝ ፡ መከታ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ጌታ (፪x)

በሰማያት ፡ ላይ ፡ ለረዴቴ ፡ የሚራመደውን
ረሃቤን ፡ ያጠገበ ፡ እኔን ፡ ያረካውን
ልመናዬን ፡ ከሰማይ ፡ ሰምቶ ፡ ዘንበል ፡ ብሎልኛል
ትላንት ፡ በለቅሶም ፡ ዛሬ ፡ በእርሱ ፡ እጅግ ፡ ደስ ፡ ብሎኛል

አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን ፡ ጌታዬ ፡ ጥላ ፡ ከለላዬ
በምድር ፡ ላይ ፡ ማን ፡ አለኝ ፡ መከታ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ጌታ (፪x)

ከአመታት ፡ በፊት ፡ የገባውን ፡ ኪዳን ፡ ሲፈጽመው
አልተውህም ፡ አልረሳህም ፡ አልጥልህም ፡ ያለው
እኔም ፡ በዚህች ፡ ሕይወቴ ፡ አይሁኝ ፡ ማዳኑን
የሰይጣንን ፡ መንጋጋ ፡ መትቶ ፡ ህዝቡን ፡ መታደጉን

አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን ፡ ጌታዬ ፡ ጥላ ፡ ከለላዬ
በምድር ፡ ላይ ፡ ማን ፡ አለኝ ፡ መከታ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ጌታ (፪x)

በጆሮዬ ፡ የሰማሁትን ፡ በዐይኖቼ ፡ አይሁ
እግዚአብሔር ፡ ከመቃብር ፡ በድኑን ፡ ሲጠራው
አለቀለት ፡ አበቃ ፡ ብዬ ፡ አዝኜ ፡ የተውኩትን
ጌታዬ ፡ ነፍስ ፡ ዘርቶበት ፡ ዳግም ፡ ሕያው ፡ ሲሆን

አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን ፡ ጌታዬ ፡ ጥላ ፡ ከለላዬ
በምድር ፡ ላይ ፡ ማን ፡ አለኝ ፡ መከታ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ጌታ (፪x)

ለነገዬ ፡ የምለው ፡ የለም ፡ ኢየሱስ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ
በምድር ፡ ላለው ፡ ኑሮዬ ፡ ከዚህም ፡ በኋላ
ለነፍሴ ፡ ባለ ፡ አደራ ፡ ዕድሌም ፡ ፈንታዬ
ሌላ ፡ መከታ ፡ የለኝም ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ ጌታዬ

አዝ፦ ተመስገን ፡ ተመስገን ፡ ጌታዬ ፡ ጥላ ፡ ከለላዬ
በምድር ፡ ላይ ፡ ማን ፡ አለኝ ፡ መከታ ፡ ከአንተ ፡ ሌላ ፡ ጌታ (፪x)