ልጆቹን ፡ ለማከማቸት (Lejochun Lemakemachet)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ልጆቹን ፡ ለማከማቸት
ጌታችን ፡ ሲመለስ
ጥሩ ፡ ስንዴውን ፡ ለመክተት
በክብሩ ፡ ሰገለፅ

አዝ፦ ያን ፡ ጊዜ ፡ የአምላክ ፡ ልጆች
በክብሩ ፡ ይደምቃሉ
ይበራሉም ፡ እንደ ፡ ዕንቆች
በግሩም ፡ አክሊሉ

ኢየሱስም ፡ የዋጀውን ፡ ገንዘብ
በደሙም ፡ የነጣ
ቅዱስ ፡ መንጋውን ፡ ለመሰብሰብ
ወደ ፡ እኛ ፡ ሲመጣ

አዝ፦ ያን ፡ ጊዜ ፡ የአምላክ ፡ ልጆች
በክብሩ ፡ ይደምቃሉ
ይበራሉም ፡ እንደ ፡ ዕንቆች
በግሩም ፡ አክሊሉ

ኢየሱስንም ፡ የሚወዱ
ታናናሾች ፡ ልጆች
ይሆናሉ ፡ ጌጽ ፡ በዘውዱ
የኢየሱስ ፡ ወዳጆች

አዝ፦ ያን ፡ ጊዜ ፡ የአምላክ ፡ ልጆች
በክብሩ ፡ ይደምቃሉ
ይበራሉም ፡ እንደ ፡ ዕንቆች
በግሩም ፡ አክሊሉ