ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ና ፡ መርምረኝ (Gieta Eyesus Na Mermiregne)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ ፣
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ና ፡ መርምረኝ
በደሌንም ፡ ይቅር ፡ በለኝ
በአንተ ፡ መንፈስ ፡ ተመርቼ
እኖር ፡ ይሆን ፡ ሁሉን ፡ ትቼ?

በዓለም ፡ ልኖር ፡ ተስፋፍቼ
ደስታን ፡ ፈለግሁት ፡ ተግቼ
ወዲያ ፡ ወዲህ ፡ ተሯሯጥኩኝ
በጨለማ ፡ ውስጥ ፡ ባከንኩኝ

አዝ ፣
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ና ፡ መርምረኝ
በደሌንም ፡ ይቅር ፡ በለኝ
በአንተ ፡ መንፈስ ፡ ተመርቼ
እኖር ፡ ይሆን ፡ ሁሉን ፡ ትቼ?

ብዙ ፡ ደከምኩ ፡ በኑሮዬ
በዓለም ፡ ብልጭልጭ ፡ ተታልዬ
ኖርኩኝ ፡ በኃጢአት ፡ ተቅበጥብጬ
አልረካሁም ፡ ሌት ፡ ቀን ፡ ሮጬ

አዝ ፣
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ና ፡ መርምረኝ
በደሌንም ፡ ይቅር ፡ በለኝ
በአንተ ፡ መንፈስ ፡ ተመርቼ
እኖር ፡ ይሆን ፡ ሁሉን ፡ ትቼ?

ሁሉን ፡ አየሁ ፡ በዓለም ፡ ውስጥ
ግን ፡ አጣሁኝ ፡ ደስታ ፡ የሚሰጥ
ወዜን ፡ ለዓለም ፡ አስረክቤ
ኖርኩኝ ፡ በመንፈስ ፡ ተርቤ

አዝ ፣
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ና ፡ መርምረኝ
በደሌንም ፡ ይቅር ፡ በለኝ
በአንተ ፡ መንፈስ ፡ ተመርቼ
እኖር ፡ ይሆን ፡ ሁሉን ፡ ትቼ?

ይህን ፡ ሁሉ ፡ ተመልክተህ
ልቤ ፡ ገባህ ፡ ይቅር ፡ ብለህ
ክብር ፡ ለአንተ ፡ ይሁን ፡ ጌታ
ከአንተ ፡ አገኘሁ ፡ ሰላም ፡ ደስታ

አዝ ፣
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ና ፡ መርምረኝ
በደሌንም ፡ ይቅር ፡ በለኝ
በአንተ ፡ መንፈስ ፡ ተመርቼ
እኖር ፡ ይሆን ፡ ሁሉን ፡ ትቼ?