ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ልበልህ (Eyesus Hoy Kef Kef Bel Libelih)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ ፣
 ::ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ልበልህ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ
ወደር ፡ የማይገኝልህ
ከሞት ፡ ያድናል ፡ ስምህ ፪X

ስምህ ፡ እንደሚፈስ ፡ ዘይት ፡ ነው
ጠልቆ ፡ ወደ ፡ ውስጥ ፡ ይገባል
የደረቀውን ፡ አጥንት ፡ አረስርሶ
ስብራትን ፡ ይጠግናል
ሽባውን ፡ አዘልለህ
የዛለውን ፡ ጉልበት ፡ ታጸናለህ
ልብን ፡ ኩላሊትን ፡ መርምረህ
ለደካማ ፡ ኃይልን ፡ ትሰጣለህ ።

አዝ ፣
 ::ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ልበልህ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ
ወደር ፡ የማይገኝልህ
ከሞት ፡ ያድናል ፡ ስምህ ፪X

በነፍስ ፡ በሥጋ ፡ ሥልጣን ፡ አለህ
የበሽታን ፡ ሥር ፡ ነቅለህ ፡ ትጥላለህ
የታወረውን ፡ ዓይን ፡ አብርተህ
የጐበጠውን ፡ ታቃናለህ
ፍፁም ፡ ድንቅ ፡ ነው ፡ ስምህ ፡ ያድናል
የተጨነቁትን ፡ በሕመም
ከድቅድቅ ፡ ጨለማ ፡ ያወጣል
ወደሚደነቅ ፡ ብርሃን ።

አዝ ፣
 ::ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ልበልህ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ
ወደር ፡ የማይገኝልህ
ከሞት ፡ ያድናል ፡ ስምህ ፪X

ጌታዬ! ስምህ ፡ ኃይል ፡ አለው
አጋንንትን ፡ ይቀጠቅጣል
ለስሜትም ፡ ከመገዛት
ከማይረባም ፡ ልማድ ፡ ያላቅቃል
ጥላቻንም ፡ አስወግዶ
ሁሉን ፡ አንድ ፡ ያደርጋል ፡ በፍቅር
መራራን ፡ ሕይወት ፡ ለውጦ
ያጣፍጠዋል ፡ እንደማር

አዝ ፣
 ::ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ልበልህ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ
ወደር ፡ የማይገኝልህ
ከሞት ፡ ያድናል ፡ ስምህ ፪X

በዕምነት ፡ ወደ ፡ አንተ ፡ የቀረበ
በሕያው ፡ ስምህ ፡ ይድናል
ከሞት ፡ ባሻገር ፡ ያለውን
የዘላለምን ፡ ሕይወት ፡ ይወርሳል
ቸሩ ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ
በዕውነት ፡ አንተ ፡ ፍቅር ፡ ነህ
ልዑል ፡ እግዚአብሔር ፡ ሆይ!
ከፍ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ልበልህ ።

አዝ ፣
 ::ኢየሱስ ፡ ሆይ ፡ ከፍ ፡ ከፍ ፡ በል ፡ ልበልህ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ተመስገን ፡ ልበልህ
ወደር ፡ የማይገኝልህ
ከሞት ፡ ያድናል ፡ ስምህ ፪X