ብሩሕ ፡ ፀሐይህ ፡ ወጥቷል (Biruh Tsehayih Wottitoal)
From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
|
ሌሎች ፡ የድሮ ፡ መዝሙሮች (Other Classic Mezmur Lyrics)
|
|
ብሩሕ ፡ ፀሐይህ ፡ ወጥቷል
ተመስገን ፡ አምላኬ
በአዲስ ፡ ተስፋ ፡ በአዲሥም ፡ ኃይል
ልስገድ ፡ ተንበርክኬ
ለክፉውም ፡ ለፃድቅም
ፀሐይህ ፡ ያበራል
እንዳንተም ፡ ርኅሩኅ ፡ የዋኅም
ልሆን ፡ ይገባኛል
በዚህም ፡ ቀን ፡ ፈቃድህን
ልፈጽመው ፡ እርዳኝ
አሳስበኝም ፡ ሕግህን
በቃልህም ፡ ምራኝ
ወዳባትነትህ ፡ ልሸሽ
በዓይንህ ፡ ጠብቀኝ
ቀንም ፡ ሲብት ፣ ሌትም ፡ ሲመሽ
የአንተ ፡ ገንዘብ ፡ ነኝ
|