በአፋችሁም ፡ በልባችሁም ፡ ክርስቶስን ፡ አመስግኑ (Beafachum Belibachihum Kristosn Amesginu)
From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
|
ሌሎች ፡ የድሮ ፡ መዝሙሮች (Other Classic Mezmur Lyrics)
|
|
በአፋችሁም ፡ በልባችሁም
ክርስቶስን ፡ አመስግኑ
ስለ ፡ እኛ ፡ ሙቶ ፡ ተኛ
ሦስት ፡ ቀን ፡ በመቃብሩ
ከመቃብር ፡ በአምላክ ፡ ክብር
ለተነሣው ፡ ዘምሩ
ስለ ፡ ዕዳችን ፡ ተቀጣልን
ጽድቁንም ፡ አወረሰን
ያ ፡ ረጃችን ፡ ከጭንቃችን
ለዘለዓለም ፡ አዳነን
በሞት ፡ ፈንታ
ሕይወት ፡ ጸንታ
ለእኛም ፡ ሕይወት ፡ ሰጠን
እኛን ፡ ምሮ ፡ ሞትን ፡ ሽሮ
ሰይጣንን ፡ ቀጠቀጠ
ኃይልም ፡ ሁሉ
በዓለም ፡ ምሉ
ለወልድ ፡ ብቻ ፡ ተሰጠ
በብርሃኑ ፡ ለኃጥአኑ
ምሕረትም ፡ ተገለጠ
ለዓብ ፡ ክብር ፡ በዚህ ፡ ምድር
የሰው ፡ ውዳሴ ፡ ይሁን
ላንዱ ፡ ልጁም ፡ እንደዚሁም
እናመስግን ፡ ምሕረቱን
ለቸር ፡ ውዱስመንፈስ ፡ ቅዱስ
እናሳርግ ፡ ውዳሴውን
|